Saturday, September 18, 2010

በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው ቁጥር ፵፫

ይህንን የቅዱስ ያእቆብን ጥቅስ እንደ እርእስ የመረጥነው  ሰሞኑን እየተካሄደ  ያለውን የምሽት መንፈሳዊ ጉባኤ ተካፍለን ካዳመጥነው መንፈሳዊ ትምሕርት በመነሳት ነው። ጉባኤው ከቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ባሻገር ባለው የኬንዋውያን ቤተክርስቲያን እየተካሄደ ያለ ሲሆን፤ ቅዳሜ ማታና እሁድ ማታም እንደሚቀጥል ለመረዳት ችለናል። ከሁለት መቶ ምእመናን በላይ ተሳታፊ የነበሩበትን ይህንን ጉባኤ ስንካፈል የተሰማን ሐዘን የጠለቀ  ነበር። በፖለቲካው ብቻ  ሳይሆን በሃይማኖትም መለያየታችን የሚያሳዝን ሆኖ ስላገኘነው። "ፈተና የሚመጣው እኮ ሰይጣን ጥንካሪያችንን ሲያይ ነው" ብለው የሰበኩት መምህር በተለይ ሰይጣን እንደማንበገር ሲያውቅ የጭቅ ጅራፉን ያወርደዋል ሲሉ ብዙ ነገር ታወሰን። እዚህ አገር እርችት ሲተኮስ ድብልቅልቁ የሚወጣው እኮ መጨረሻው ላይ ነው ብለን አሰብን። ታዲያ በአሁኑ ሰዓት በአንድ ወገን  በጥቂት የቤተክርስቲያን አመራር ክፍልና በጣት በሚቆጠሩ ደጋፊዋቻቸው በአንጻሩ መብታችንን አናስደፍርም በካህን ታጅበን እንጂ በፖሊስ ተከበን አናመልክም በሚሉ ምእመናን መካከል የተጀመረውን መተናነቅ ስናስተውል  እውነትም ፈተናው አስከፊ እንደሆነ ታየን። ከግንድ የተገነጠለ  ቅርንጫፍ እንደሚደርቅ  አትጠራጠሩ ብለው ያስተማሩት አባት ደግሞ ለመለምለም የወይን ዛፉ አካል መሆን እንዳለብን በምሳሌ ከማስተማራቸውም በላይ፤ የማይሆን የዛፍ ተቀጽላም ከዚያም አልፎ ተገድራም መሆን እንደሌለብን ሲያስተምሩ የሚያስተምሩት የኛን  ችግር ተረድተው ይመስል ነበር። ቆይተን እንደተገነዘብነው ግን ተናጋሪው ያስተምሩ የነበረው ከሃይማኖት መራቅ እንደሌለብን ሆኖ አገኘነው። የወንጌል ትልቁ ጉልበቱ ደግሞ በተሰማ  ቁጥር ከራስ ችግር ጋር፤ ከምናየው ጋር ሁሉ መመሳሰሉና ለዛም መልስ ይዞ መገኘቱ ነው። ታዲያ ቤተክርስቲያን እንደሌለን ተከራይተን ክርስቲያን እንዳልሆንን ሁሉ ተለያይተን መገኘቱ ካስደሰተን ያስተማሩን አባት እንዳሉት እራሳችንን ዞረን መመልከት ሊኖርብን ነው። እኛ ይህንን ገምግመን መስቀል ካልገዛው ሕግ ይዳኘው ብለው የተነሱትን ደግፈናል። የለም ካህናት መሰደብ አለባቸው፤ ምእመናን መታሰር ይኖርባቸዋል፤ የተዋጣው ገንዘብ ካለ እስኪያልቅ እንዋጋለን ሲያልቅ ቤቱን እንሸጣለን ከሚሉት መወገን የምንል ካለን መወገን። ካልሆነ እንደ ክርስቲያንነታችን  ባመንበት ጸንተን በእምነታችን ሳንደራደር ለመብታችን ቆመን  የሕግን የበላይነት የተቀበልን መሆን ይኖርብናል ብለን የምናምን ተጠናክረን መነሳት ይኖርብናል እንላለን። የኛ ችግር በመብት እረገጣ ላይ ነውና ለዚህ ደግሞ ከሕግ ውጭ መፍትሄ ይኖራል ብለን አናምንም። የሃገራችን ልማድ ተከትለን  በሽማግሌ ለመፍታት ካንዴም ከአራት ከአምስት ጊዜ በላይ እንደተሞከረ ሁላችሁም የምታውቁት ጉዳይ ነው። ከሳሾቹ ችግሩን ለመፍታት ሽማግሌዎችን አክብረው ተቀምጠው ተወያዩ። የቤተክርስቲያን አንባገነን መሪዎች ግን ገደል ግቡ አሉ። ይባስ ብለው ፖሊስ ቀጥረው ውሻ አሳጅበው ሊያስፈራሩን ተነሱ። በብሎጋቸው ላይ የቤተክርስቲያኑን አንጋፋዎችና መስራቾች አንተ  እያሉ መዝለፍ ጀመሩ። ማ ከማ ጋር ወሲብ እንዳደረገ ማ እንዴት ልጅ እንደወለደ ማ ምን የፖለቲካ አመለካከት እንዳለው ዘገቡ። ካሕናቱን እንደ ሰፈር ዳንዴ ፈረጁ በወሲብ ከባለትዳር ግለሰብ ጋር በመጠርጠር ስም አጠፉ። ይህንን ሲያደርጉ ትዳር እያፈረሱ ቁርባንን እያረከሱ መሆኑ ግን አላስጨነቃቸውም። ዘር ቆጥረው የመንግስት ደጋፊ ናቸው ብለው ትላንት አብረዋቸው የነበሩትን እየተገባበዙ የበሉበትን ሳህን እየሰበሩ የጠጡበትን ጽዋ እየደፉ ታዩ። መንግስትን መደገፍ መብት መሆኑ ግን አልተገለጸላቸውም። ይህን ሁሉ አድርገው ታዲያ  ታዛቢያቸው በዛ እንጂ ደጋፊያቸው እንዳልጨመረ በሚካኤል ስም መመስከር ይቻላል። ያ  አልበቃቸውም

ካህናትን ሊያዋርዱ ተነሱ ከሸፈ።
በዘር መጡ ተመቱ።
በፖሊስ መጡ ተረቱ።
በፖለቲካ ተንቀሳቀሱ ፈራረሱ።
በገንዘብ ተመኩ ቋቱ እየደረቀ  መጣ።
በጉልበት መጡ ጉልበት የሚካኤል ሆነባቸው።
ዛሬ የቀራቸው ለቡድናቸው የሰጡት "የሚካኤል ሰይፍ" የሚለው ስም ብቻ ነው። ያ ደግሞ  የድሮውን የቻይና  ግሩፕን ያስታውሰናል። 
ወንድሞችና  እህቶች
"ከራበው ልጄ  ይልቅ ለጠገበው ልጄ  አስባለሁ"  ያሉት ዳላስ ነዋሪ የሆኑ ቤተሰቦች አልነበሩም። አባባሉ የቆየ  ነው ለማለት ነው።የራበው ልጅ እቤት ተኮራምቶ ይቀመጣል የጠገበው ግን ማን አለብኝ ብሎ ይደባደብና  ወይ ነፍስ ያጠፋና ቤተሰቡን ችግር ላይ ይጥላል ለማለት ነው። እዚህም በዳላስ አካባቢ ታዲያ ከላይ እንደጠቀስነው ሰላም ሲሰፍን እንቅልፍ የሚነሳቸው የሕዝቡ መፋቀር የሚያናድዳቸው፡ ከመጋረጃ ጀርባ ተደብቀው ሲናገሩ በድምጻቸው የማይታወቁ፤ በብእራቸው የማይለዩ፤ በተግባራቸው የማይፈረጁ የሚመስላቸው ግለሰቦች ከትላንትናው ቁጥራቸው እየመነመነ እርስ በርሳቸው እየተወነጃጀሉ ለመሆኑ ብዙ ፍንጭ እየየን ያለ  ይመስለናል።  በዚህ በከተማችን ለእምነታቸው የቆሙ ትክክል አይደለም ብለው ያመኑትን የተናገሩ ዲሞክራሲ በሰፈነበት አገር መብታችንን አናስደፍርም በጥቂት አንባገነኖች አንገታችንን አንደፋም መብታችንን  የሃገሩን ሕግ ተጠቅመን እናስከብራለን ባሉ "ቅዱሳን ነን"በሚሉ ተሰድበዋል "ከኛ ወዲያ ክርስቲያን የለም"  በሚሉ ተዘልፈዋል። ያም ሆኖ ግን የተዋረዱት ሰዳቢዎቹ እንጂ የተሰደቡት አልነበሩም።

ባለፈው እንደተናገርነው ሁሉ ማንነታቸውን እያወቅን ስም ጠርተን፤ ድክመታቸውን ፈልፍለን፤ የመኝታ ቤታቸውን ምስጢር አውጥተን ለአንባብያን አላቀረብንም። ያን ባለማድረጋችን ፈሪዎች ተብለን ይሆናል። እኛ ግን በደረቅ መሬት በመጓዛችን እንደነሱ በማጥ ውስጥ አልዳከርንም። ለቤተክርስቲያንናችን በ ሺህ የሚቆጠር ገንዘባቸውን ያፈሰሱ ምእመንን በስድብ ውርጅብኝ የገረፏቸው ግለሰቦች እነማን እንደሆኑ እናውቃለን። ግን ማንነታቸውን በመናገር እነሱን ማስተዋወቅ ደግሞ ለነሱ ክብር እንደሚሆን ስለተሰማን እንዳላወቅን አለፍናቸው። ባለፈ በመረዋ እትምታችን እንደተናገርነው ለአንባብያን ፍንጭ እንዲሆን የተሰደቡትን አባላት ስትለዩ የሚሳደቡት እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ደቂቃ አይፈጅባችሁም። እኛ መልእክቱ እንጂ መልእክተኛው ምን ያደርጋል በሚል እራሳችን ማስተዋወቅ አልወደድንም የመደበቅ ፍላጎት ኖሮን እንዳልሆነ ግን ምስክራችን ሚካኤል ነው። በምንም ሰዓት በሃሳብ ላይ በመታገል እንጂ በስድብ ለውጥ ተገኘ ሲባል ሰምተንም አይተንም  አናውቅምና መሳደብን እንደመሳሪያ መጠቀም አልፈለግንም። መኪናችን ቢሰበር የሚጎትትልን ሰው እናጣለን ብለን ሰግተንም አናውቅ። እንጀራ ንግድ ውስጥ ስለሌለንበት ደግሞ የደንበኛ ልምምጥ የለብንም። ገንዘቡና ጊዜው በተገኘ እንጂ አውሮፕላን ጣቢያ የሚያደርሰን ይጠፋል ብለን አንጨነቅም። ለቦርድ የመመረጥ ፍላጎት ስለሌለን ማን ይመርጠናል ብለን አንሰጋም። ሌሎች እንደሚያደርጉት የራሳችንን የቤተሰባችንን ገድል እያወራን ቅዱስነታችንን እየተናገርን ለምርጫ እንዳትረሱን አንልም። የቤተክርስቲያን ስራ በልመና ለብቁዎች የሚሰጥ እንጂ በቅስቀሳ ምረጡኝ ሲባል ጥቅም አለበት እንዴ? ሊያሰኝ ይችላልና።
አገር ቤት ያልተሳካ ፖለቲካ ዳላስ ያለውን ምእመን በማመስ በለስ ሊቀናን ይችል ይሆናል ብሎ  ማለም ደግሞ በፖለቲካ አለመብሰል ይመስለናል።

የሚያስጨንቀን ነገር ቢኖር ያልነበሩ ሲመሰክሩ ያልከፈሉ የከፈሉትን አባቶች ሲያዋርዱ ያደጉበት አስነዋሪ ጠባያቸው በስተርጅና  ሲያገረሽባቸው ስናስተውል ነው። 

የሚያስጨንቀን "ክርስቲያን ነን" እያሉ አዛውንቶችን፤ መንፈሳውያን ነን እያሉ ወንድም እህቶችን የመንደር ዱርዬ እንኳን በማይጠቀምበት አስነዋሪ ቃላት ሲሳደቡ መስማታችን ነው።
እኛ የሚያስጨንቀን በሕዝብ ገንዘብ ንጉሥ ሆነው ባልከፈሉበት አዛዥ ባላጠራቀሙት በታኝ ባልሰበሰቡት ወሳኝ መሆናቸው ነው።የሚያስጨንቀን ክርስቲያንን አባረን የክርስቲያን ስብስብ  ነን ሲሉ ስንሰማ ነው።

የሚያስጨንቀን በሬ  ወለደ  ብለው ሲያወሩ ነው።

ትላንት ለኢትዮጵያ  ቀን እንዳትሄዱ ሲሉ ከርመው፤ የኢትዮጵያ  ቀን ሳይሳካ  ቀረ  ሲሉ ሰንብተው፤ መረዋ የነበረውን ለአንባብያን ሲተነትን ገንዘብ ያዋጡትን ግለሰቦች ስም ሳይቀር ሲናገር ውሸታቸው መጋለጡን ሲገነዘቡ አቶ ሰይፉ ካሉበት አቶ  መደቅሳ ከገቡበት ችግር የለብንም ብለው መናገር ጀመሩ። ባንድ አፍ ሁለት ምላስ ይሏችኌል ይህ ነው። የወያኔ ቀን ነውና እንዳትሄዱ ብለው በጻፉት ብእራቸው፤የቅዳሜው እለት አልተሳካም እሁድም የተገኙት የእድር ሰዎችና ቤተሰቦች ብቻ ናቸው እንዳላሉ መረዋ ገንዘብ ያዋጡትን ከፊል ስሞች አውጥተው ሲያዩ ተደናገጡ። ግለሰቦቹን እንዳይሳደቡ ደግሞ ገንዘብ አዋጡ ተብለው ስማቸው ከተጠቀሰው አንዳንዶቹ በቤተክርስቲያኑ ጉዳይ ቢያግዟቸውም በመረዳጃ መሃበሩ ጉዳይ ላይ ያላቸውን አመለካከት እንደማይጋሩ የተገነዘቡት ሆነ። ታዲያ እነሱን ቢሳደቡ ጸሐፊዎቹ እነማን እንደሆኑ ስለሚያውቌቸው የሚመጣባቸው ችግር ስለታያቸው ሕዝቡም እየሸሻቸው መምጣቱን ሲገነዘቡ ተገልብጠው መልካም ጅምር ነው ማለት ጀመሩ። ሃሌ ሉያ። የሚደገፍ አቋም ነው። ይህንን ስላደረጉ ደግሞ  እኛ እነሱ በሄዱበት ጎዳና በምንም አይነት አንደማንጔዝ ቃል እንገባላችኋለን። የኛን መንገድ ሲቀላቀሉ ደግሞ ደስተኛ እንሆናለን እንጂ ለምን አጣበባችሁን ብለን አንከፋም። በብሎጋቸው የጻፉትን አንስማማበትም አቶ ዮሴፍ ላይ የተጻፈው የኛ አቌም አይደለም አሉና አረፉት። አሁንም ግን ስለ ጋሼ ሃይሉ የተጻፈውን አልኮነኑም። ስለፍቅረማርያም ያወሩትን አልኮነኑም፤ ስለ  አዜብ የተሳደቡትን ይቅርታ  አልጠየቁበትም፤ ስለብዙአየሁ ያወሩትን አላፈሩበትም፤ ስለ አቶ ጌታቸው ትርፌ በተደጋጋሚ ያወጡትን እንደኮሩበት ነው። ስለፈትለወርቅ  የተናገሩት አላሳፈራቸውም። ስለ ተፈራወርቅ የጻፉትን ይኮሩበታል ማለት ነው። ስለአቶ  ተኮላ የዋሹትን አልተሸማቀቁበትም። ጥሩአየር ሲዘልፉ ምን ማለታቸው እንደሆነ እራሳቸውም ግራ የተጋቡ ለመሆኑ ያወቁት አይመስለም።  አቶ ግርማቸውን በመሳደባቸው አሁንም ትልቅ የሆኑ እንደመሰላቸው ነው። ስለሙላው ሲዘባርቁ ያሸነፉ እንደመሰላቸው ነው። ስለ  ጸሃይ ጽድቅ ወንጀል ሲያወሩ የሚያስከትለው  ምን ይሆን? ብለው አልነበረም። ከሁሉም የሚገርመው ዳዊት አለማየሁን በዘሩ ሳይቀር ተሳድበው እንቅልፍ ወስዷቸው ካደረ ወንድሞቼ  እነዚህ ሰዎች ወንጀለኞች ናቸው። ብዙ መጥቀስ ይቻላል። ስለተሳደቡ ግን አላሸነፉም እንደምታዩት እየተሸነፉ መጡ እንጂ። ከሁሉ የገረመን ለቤተክርስቲያኑ ገነዘባቸውን ያፈሰሱት አቶ  ሃይሉና  አቶ  ምናሴ የስድብ ውርጅብኝ ሲያወርዱባቸው ተዋቸው እንሱን በፍቅር መዋጋት ብቻ ነው ያለብን ብለው ሲናገሩ ስንሰማ ነው። ያንዳንዱን የመንፈስ ደካማነት በማየት የሚያዝን ሰው በሌላው ጥናት ይጽናናል ማለታችን ነው።
ዛሬ እርስ በራሳቸው እየተላተሙ ነው። ነገ አቀርቅረው እንደሚቀሩ ደግሞ ምንም ጥርጥር የለንም።
የሳምንት ሰው ይበለን 

Saturday, September 11, 2010

መልካም አዲስ ዓመት

መልካም አዲስ ዓመት
                              ዘመነ ማርቆስ ተሻረ፤
ዘመነ ሉቃስ ተሾመ።    

አዲሱ ዘመን ሐሰት የሚጨነግፍበት
እውነት የሚለመልምበት ዘመን እንዲሆንላችሁ መርዋ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል።

Wednesday, September 8, 2010

ያያችሁት ሰው ሳይሆን ጥላ ነው ለሚል ሰው መድሃኒቱ የምን ጥላ? ብሎ መጠየቅ ብቻ ነው። ቁጥር ፵፪

በስደት ላይ 30 ዓመት እየሞላን ነው ብሎ  መናገር የሚያስደነግጠው አዳማጩን ሳይሆን ተናጋሪውን ለመሆኑ ቋሚ ምስክር ነን። ምን ስትሰሩ ከረማችሁ ለሚሉት አጥጋቢ መልስ መስጠት ያስቸግራልና። ስለ እውነት ለመናገር እንደ ቀልድ ያለፈው የስደት ዘመን የራሱ የሆነ  ውጣ ውረድ ነበረበት። ዛሬ እንደቀልድ የምናየው ነገር ትላንት የተራራ ያክል አስቸጋሪ እንደነበር ሲነገር ቀልድ ሊመስል ይችላል። ዛሬ የምንምነሸነሽበት ነፃነትና የግለሰብ መብት ትላንት በነበሩ የአሜሪካውያን ታጋዬች ደም የተገነባ መሆኑን መቀበል የሚከብደን ብዙዎች ብንኖር አይገርምም። በወቅቱ የነበረውን ዘረኝነት በምስክርነት የሚናገሩ ሰዎችን ስንሰማ እንኳን ድግግሞሽ ነው በማለት ማዳመጡ ሁሉ የሚያስጠላን  ልንኖርም እንችል ይሆናል።  የራሳችንን ጉብዝና እያጎላን የሌላውን ስንፍና መናገራችንም ያለ እውነታ  ነው። በዚህ በምንኖርበት አገር ዘረኝነት መኖሩን ለመቀበል ደግሞ  እራሳችን ችግር ውስጥ ገብተን መገኘትን አለብን። ካልሆነ የሌላው ስንፍና  እንጂ ለምን እኛ ከባሕር ማዶ  መጥተን ከነዋሪው መሰላችን የተሻለ  ኑሮ እንኖራለን ብለን የምንከራከር እንዳለን መካድ የሚያስገምተው እራሳችንን ብቻ ነው።

ዛሬ ይህንን ለማንሳት ያነሳሳን ሁሉም ነገር ጊዜውን እየጠበቀ ትላንት ሌላው እደረሰበት ዛሬ እኛም ለመድረሳችን ብልጭታ  እያየን በመምጣታችን ነው። የጽሑፋችን መነሻ  የሆነን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ  ተደርጎ  የነበረው ፱ኛው የኢትዮጵያ ቀን ላይ ያየነው ቅንነት የተሞላበት መሰባሰብ ነበር። በዓሉን ለማክበር የመጡት በሞላ አንድ ዓይነት አመለካከት አንድ ዓይነት የፖለቲካ አቋም ነበራቸው  ለማለት  ባንደፍርም መደረግ አለበት በሚባለው እቅድ ላይ ግን ምንም ልዩነት እንዳልነበረ በስፍራው ነበርንና ምስክርነት መስጠት እንችላለን።

ባለፈው በመረዋ እትምታችን ስለ ቅዳሜው የዘገብነው  እንዳለ ሆኖ እሑድ እለት የተገኘው ሕዝብ ቁጥር ከቅዳሜው የላቀ  ከመሆኑም በላይ በሁለቱ ቀን ጊዜ  ውስጥ $78,000  ለማዋጣት ቃል መገባቱን ግማሾቹም መክፈል መጀመራቸውን ስናይ የኢትዮጵያ መረዳጃ ማህበር አዳራሽ እውን እንደሚሆን ለመቀበል ጊዜ አልወሰደብንም።

ከሁሉም በላይ የሚካኤል ቤተክርስቲያን ሲገዛ በግንባር ቀደምትነት ያስተባበሩትና እዳው በጥቂት ዓመታት ተከፍሎ እንዲያልቅ ያስደረጉት አቶ ሰይፉ ይገዙ በፈቃደኝነት የዚህም የመረዳጃ ማህበር የሕንፃ ኮሚቴ አባል መሆናቸውን ስናይና በእለቱ ይህ ትላንት መደረግ የነበረበትን ሕልም ዛሬ እውነት ለማድረግ የተቻላቸውን ለማድረግ ቆርጠው መነሳታቸውን ቃል ሲገቡ ስንሰማ ይቻላል የሚለው መፈክር በጆሮአችን መደወል ጀምሮ ነበር። የኮሚቴው አባላት ስም ሲጠራም የጅምሩ እውነተኛነት የባሰውን እየጎላ  መጣ። እንዴው የመሃበሩን ሥራ  መጋፋት ነው ባትሉን ለአንባብያን ማንነታቸውን እናስተዋውቃችሁ።

1  አቶ  ሰሎሞን  ሐመልማል (የቦርዱ ተወካይ)
2  አቶ ሰይፉ ይገዙ
3  አቶ  በትሩ ገብረእግዚአብሔር
4  አቶ  ግርማቸው አድማሴ
5  ወይዘሮ ተዋበች
6  አቶ ሚደቅሳ በየነ
7  አቶ  መላኩ አቦዝን
8  አቶ ዳንኤል ግዛው   እንደሆኑ ልንገልጽላችሁ እንወዳለን።

በዚህም እለት በተደረገው የገንዘብ ማሰባሰብ ቃል የገቡትንና  የከፈሉትን ሥም ዝርዝር ከምናስታውሰው  ብንጠቅስ ስብስቡ የተለያየ  ክፍልን ያቀፈ  ለመሆኑ ግንዛቤ  የሚሰጥ መሰለን።

አቶ ብርሃን መኮንን እና ባላቤታቸው ወይዘሮ ተዋበች   $10,000
አቶ ኤልያስ                                                       $6,000
አቶ  ሃይሉ እጅጉ                                                $5,000
አቶ  ብዙአየሁ      (በ city shuttle )                     $5,000
አቶ ሙላው ወራሽ                                              $5,000
ዶክተር ስዩም                                                                               $1,000
አቶ ሃብቴ                    (በማሩ ግሮሰሪ ስም)               $1,000
አቶ መንግስቱ ሙሴ   (በአበባ  ግሮሰሪ ስም)              $1,000
አቶ  ሰይፉ ይገዙ                                                $1,000
አቶ ግርማቸው አድማሴ                                       $1,000
አቶ አበበ ጤፉ                                                   $1,000
አቶ መላኩ አቦዝን                                               $1,000 ለማዋጣት ቃል መግባታቸውን ስንነግራችሁ በርካታ ግለሰቦች በነፍስ ወከፍ $500 - 100  መለገሳቸውንና ቃል መግባታቸውን ለማየት ችለናል። በአጠቃላይ በበዓሉ ላይ በድምሩ $78,000   ቃል እንደተገባ ገሚሱም ገቢ እንደሆነ ከኮሚቴው በተሰጠው ገለጻ ለመረዳት ችለናል።
ታዲያ  እነዚህ ግለሰቦች በሙሉ የፖለቲካ ሰዎች ወይም ስብስቡን  እንደሚቃወሙት  ግለሰቦች አባባል አገር ቤት ካለው መንግስት ድርጎ ፈላጊዎች ናቸው ብሎ መወንጀል ከተቻለ  ፍርዱን ለአንባብያን እንተዋለን::

በወቅቱ ለበዓሉ ድምቀት የሰጡት የጋርላንዱ ከንቲባ የመረዳጃ መሃበሩ ያዘጋጀውን ሽልማት ለተሸላሚዎች ከመስጠታቸውም በላይ በግላቸው መዋጮ ማድረጋቸውን ሳንናገር አናልፍም። አርክቴክ የሆኑትና  መሃበሩን በቦርድ ተመራጭነት የሚያገለግሉት  አቶ አብርሃም ተሰማም ለዚህ ሕንጻ መሳካት ይረዳ ዘንድ የሕንጻውን ንድፍ በነጻ እሰራለሁ በማለት በሺህ የሚቆጠረውን ወጪ ገምድለው ጥለውታል። ሁኔታውን የታዘቡት የእለቱ የኪነት አቀንቃኝ አቶ ይሁኔ በላይም ለሚመጣው የገንዘብ መዋጮ ስብስብ ቀን በነጻ እንደሚዘፍኑ ለተሰበሰበው ሕዝብ ቃል ገብተዋል።

በማጠቃለያ እንደቆየው የቻይኖች አባባል "የሺ ማይል ጉዞ  በእርምጃ  ይጀመራል" ነውና ባለፈው በታዘብነው ግን ከማይል በላይ መጓዝ እንደተቻለ  ለመመስከር ችለናል።

ሰው አልነበረም ለሚሉት ታዲያ እንደ አርእስቱ ሁሉ ይህ ታዲያ ከየት መጣ? ልንልላቸው እንወዳለን

በዚህ አጋጣሚ ለመላው የስልምና ተከታዬች መልካም የረመዳን በዓል በመረዋና  ባንባቢዎቻችን ስም እንመኝላቸዋለን::

የታሰበውን  ለማስፈጸም ይርዳን እያለ መረዋ ለዛሬ በዚህ ይሰናበታል።

Sunday, September 5, 2010

ከማያዳምጥ ጋር መወያየት ትርፉ የእራስን ቃል መልሶ ማዳመጥ ብቻ ነው። ቁጥር ፵፩

ደህና  አደራችሁ ሳይሆን "ደህና ያደራችሁ አላችሁ?" ብለው ይጠይቁ የነበሩ ግለሰብ እንደነበሩ ያወጉኝ አዛውንት በገበያ መሃል ቀን በቀን ፋኖስ ይዞ ሲጓዝ የነበረን የድሮ ፈላስፋ ምን እየሰራህ ነው? ተብሎ ሲጠየቅ  ሰው እየፈለግሁ ነው ማለቱንም እያስታወሱ ነበር። እንዴው ለልማዱ እንዴት ከረማችሁ?እንበል እንጂ ያለፉት ሳምንታት እንዲሁ ሕብረተሰባችን እየታመሰ ተሳዳቢዎቹ ስድባቸው አልቆ እባካችሁ የምንዘልፈው አልቆብናልና ያላችሁን ላኩልን እያሉ ሲማጸኑ የሰማንበት ወቅት እንደነበረ ሁላችሁም የታዘባችሁት ጉዳይ ነው።

በሌላ ወገን ደግሞ ይሳደቡ የነበሩት ስድቡ ማንንም እንዳልሳበላቸው ሲረዱ አሁንም ከመንበሩ ሆነው ከደሙ ንጹሕ ነን ማለታቸውን ስንሰማ፡ አልተደነቅንም። ይህ እንደሚሆን እናውቅ ነበርና። ሰዳቢዎቹን ይደግፉ የነበሩት ሁኔታው መስመር ማለፉን ሲገነዘቡ ይህ መቆም አለበት በማለታቸው እነሱም የስድቡ ጅራፍ እየደረሳቸው ለመሆኑ በአካል ቀርበው ያነጋገሩን እንዳሉ ስንነግራችሁ እሰየው ብለን አልነበረም። ስንሰደብ የተሰማንን እያስታወስን ድጋፍ ሰጠናቸው እንጂ። እኛ ደስተኛ የምንሆነው አሁንም የስድብ ሙዚቃ የሚማርካቸው ዘላፊዎች በተራቸው አሁንስ በቃን ሰውም አልወደደልን ፈጣሪንም አስቀየምን የሚሉበት ቀን ሲመጣ ብቻ  ነው። ያ ደግሞ እሩቅ እንዳልሆነ  ብዙ ፍንጭ እያየን ይመስለናል።

ሁላችሁንም ልንጠይቅ የምንወደው ለስድባቸው ጆሮ በመንፈግ የሚሉትን ባለማራባት አዳማጭ እንዲያጡ ለማድረግ እንድትተባበሩን ሲሆን፤ አድማጭ ሲያጡ እርስ በርሳቸው እየተሰዳደቡ እንደሚለያየዩ እርግጠኛ በመሆን ነው። ገበያተኛ የሌለበት ጠጅ ቤት ሰካራሙ ሰራተኛው ብቻ ይሆናል ይባላልና። 

በቤተክርስቲያናችን የስደት ሲኖዶስን ለማስገባት የሚደረገው ጥድፊያ እየታየ  ሲሆን፤ ባለፈው እንደነገርናችሁ ድቁና ለማግኘት ወደ ሂውስተን ተልከው የነበሩትን ሕጻናት ለድቁና መብቃታቸውን በደብዳቤና በስልክ ያረጋገጡት የሚካኤል ካህን ይህንን ሲያደርጉ ምን ማለታቸው እንደሆነ ለናንተ  መንገር አይኖርብንም። መልሱ ለሁላችሁም ግልጽ ነውና። በደብዳቤ  እውቅና  ሰጥቶ እከሌን ሹምልኝ እያሉ እኔ ገለልተኛ ነኝ ማለት ደግሞ  "አጨስኩ እንጂ አልዋጥኩትም"  የሚለውን  ያለፈ የአሜሪካ ባለስልጣን አባባል ያስታውሰናል። ይህ ቤተክርስቲያን በሬሳችን ላይ እንጂ በሕይወት እያለን ለስደት ሲኖዶስ አይሰጥም ይሉ የነበሩትን አዛውንቶች በሉ መሞቻችሁ ይኸው ተቃረበ ለማለት አንወድም፡ መሞታቸውን አንፈልግምና። ይልቁንስ ድቁና የሚሰጡት የስደቱ ሲኖዶሶች ከሆኑ ልጆቻችንን አንልክም ብለው አቋም የወሰዱትን ቤተሰቦች መረዋ በዚህ አጋጣሚ  ስም ሳይጠራ አድናቆቱን ሊገልጽ ይወዳል።    

በሌላ መንገድ ተሳዳቢዎቹ የመሳደብ መብት እንዳላቸው የአሜሪካን አገርን ሕገ መንግስትን በመጥቀስ በተደጋጋሚ ሲናገሩ አድምጠናል። እንዴው አተካሬ  ላለማብዛት ልንተወው ፈለግንና አላስችል አለን። አንድ ሰው በሕግ እራስን ለመከላከል መግደል እንደሚችል ተደንግጓል ያ ማለት ግን ሰው መግደል ይቻላል ማለት አለመሆኑን ቢገነዘቡ መልካም ነው። 

ስለፍቅር የሚሰብኩ ቤተክርስቲያን ለምን ይከሰሳል የሚሉ የስደት ሲኖዶስም ደጋፊ አለውና ስለነሱ ባትናገሩ ጥሩ ነው ብለው የድርጅታቸውን ኦፊሻላዊ የአቋም መግለጫ የሚያስተጋቡ አሁንም ነገሮች በውይይት መፈታት አለባቸው የሚሉ መጣጥፎችንም ተመልክተናል። "በፍርድ ቤት ሰላም አይመጣም ማንም ቢያሸንፍ ሁላችንም ተሸናፊዎች ነን"  ብለን በመረዋ ተከታታይ እትምቶቻችን የምንናገረው ስለነበረ  እንኳን ለዚህ አበቃችሁ  እንኳን እውነታው ተገለጸላችሁ ከማለት በስተቀር አባላችንን ኮረጁት  ብለን አልተናደድንም።

ለናሙና ያክል ካለፈ መረዋ  እናካፍላቸው።

........አሁንም ለማንም ይፈረድ ለማንም ሁላችንም ተሸናፎዎች ነን ብለን እናምናለን። ፍርድ ቤት ይፈርዳል ግን ለማንም ይፍረድ ለማን አንድ እንሆናለን ወይ?ነው ጥያቄው። የተፈረደለት ይፈነጥዝ ይሆናል፤ ሰላም ፍቅር መጣ ማለት ግን አይደለም። ሰላም የሚፈጠረው፤ አንድነት የሚመጣው መነጋገር ሲቻልና ልዩነቶችን በጋራ ተወያይተን መፍትሄ ስናገኝላቸው ብቻ ነው።

ሴትዬዋ እርጉዝ ነች እሚለው ላይ ከተስማማን፤ መውለዷ የግድ ነው እዛ ላይ መከራከር አያስፈልግም የሚያዋልዳት ዶክተር የሚረዳት፤ ሆስፒታል እስካለች ጊዜ ብቻ ይሆናል። ወልዳ እንዴት ማሳደግ ትችላለች እሚለው ላይ ግን የዶክተሩ ሚና አይኖርም ለማለት ነው። በዛ ላይ ሚና መጫወት የሚችሉት ቤተሰብና ዘመድ ጔደኛና የሰፈር አዛውንቶች መሆናቸውን መካድ እንዴት ይቻላል? ካልተግባባን ሌላ ችግር አለ ማለት ነው። ስለሆነም በቤተክርስቲያናችን ሰላም መውረድ የሚችለው ሁላችንም ከልህና ከቁጭት ወጥተን በመነጋገርና በመመካከር ብቻ ነው። ወንድሞችና እህቶች ይህ የእምነት ስብስብ መሆኑንም አንዘንጋ።

በሌላ እትምታችን ደግሞ በመረዋ ቁጥር  ፲፫ ።

1 ሕጉ ወደ ነበረበት መመለስ አለበት
2 አባላት ያለምንም ጥያቄ መክፈል የሚችሉትን እየከፈሉ መመዝገብ አለባቸው።
3 የቦርድ አባላት ነን ባይ አንባገነኖች ሕዝቡ ለመረጣቸው ጊዜአዊ ኮሚቴ አስርክበው መውረድ አለባቸው።
4 የሚደረገው ስብሰባ በገለልተኛ ምእመናን መመራት ይኖ ርበታል ብለን እናምናለን።

በተጨማሪም በመረዋ ቁጥር ፲ " ዝምታ በራሱ ተቃውሞ ነው" የሚለውን በከፊል እንጥቀስ።

ቤተክርስቲያናችን ወደ መፍረሱ እየተቃረበ ለመሆኑ ሁሉም የተስማማበት ጉዳይ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት። ይህንን መጥፎ ሂደት ለመግታተ የሚቻለው የሚከተሉት ማረሚያውች ባፋጣኝ ሲደረጉ ብቻ ነው ብሎ ያምናል።
1 ቦርዱ በጊዚያዊ ኮሚቴ ሲተካ
2 የቀድሞ አባላት ወደ አባልነታቸው እንዲመለሱ ሲፈቀድ
3 ተቀየረ የተባለው የአንባገነን ሕግ ተሽሮ ወደ ድሮው ሕግ ስንመለስ
4 ቤተክርስቲያኑ የአምልኮ እንጂ የፖለቲካ ስፍራ መሆኑ ሲቆም
5 የእምነትን ጉዳይ ካህናቱ ብቻ መምራት ሲችሉ
6 የቤተክርስቲያን ገንዘብ የሰረቁ ምህረት ሲደረግላቸው ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
ይህ ካልሆነ ቀጣዩ ትግል በዝምታ መሆን አይችልምና ዝምታ በራሱ ተቃውሞ መሆኑ ቢገባንም ተሰብስበን በመነጋገር መፍትሄ መፍጠር አለብን በማለት ጥሪ ማድረግ እንወዳለን። "  የጥቅሱ መጨረሻ 

ይህ ታዲያ የመረዋ የቆየ  አቋም ብቻ  ሳይሆን አሁንም የምንታገልበት መርህ መሆኑን በ ድጋሜ ማስረገጥ  እንወዳለን።

ከቤተክርስቲያን ባሻገር በትላንትናው እለት 9ኛውን የኢትዮጵያ ቀን ለማክበር ሄደን ጥሩ ምሽት ማሳለፋችንን ስንመሰክር፤ የዳላስ ፎትዎርዝ አካባቢ ፍልሰታቸው ከኢትዮጵያ  የሆነ ሁሉ የሚገናኙበት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለመገንባት የተጀመረው ሥራ ግቡን እንደሚመታ ከኮሚቴው አባላቱ ገለጻና  በወቅቱ ከነበረው የሕዝብ የገንዘብ ችሮታ እሽቅድምድሚያ በመነሳት ድምዳሜ ላይ ደርሰናል። መረዋም የኮሚቴው ጥረት ግቡን  ይመታ  ዘንድ ሁላችንም መተባበር እንዳለብን ሊያሳስብ ይወዳል። ባንሳሳት በውቅቱ ቃል የተገባው ከ $50000 በላይ ገንዘብ በጥቂት ጊዜ ውስጥ የእጥፍ እጥፍ እንደሚሆን  ጥርጥር የለንም።

እንዲሁ ካካባቢው ሳንወጣ በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በምእመናን የተቋቋመው የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ልሳን የሆነ  ብሎግ መፈጠሩንና  ብሎጉም በጅምር ላይ መሆኑን የደረሰን ዜና ያረጋግጣል። ለብሎጉ እድገት ኮሚቴው ትብብራችሁን እንደሚጠብቅም ተነግሯል። 
 http://www.meleket4u.blogspot.com/

 እውነትን የያዘ ማሸነፉ የግድ ነው
መልካም ሳምንት።