Thursday, July 14, 2011

የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጠ

ውድ ምእመናን እንደምን ከረማችሁ እኛ በፈጣሪ ቸርነት እስካሁን አለን። ምነው ጠፋችሁ?  ብላችሁ ለጠየቃችሁን መልእክት ለጻፋችሁልን ሁሉ አለን ክብሩ ይስፋ ለመድኅኒዓለም  እንላለን። ከ ሁለት ቀን በፊት የ5ኛው districte ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በወይዘሮ  ጥሩአየርና  በአቶ ዳግም በተመሰረተው የቦርድ አባላት ያለአግባብ የስልጣን አጠቃቀም ክስ ላይ ብይን መስጠቱን ለአንባብያን መናገር እንወዳለን። መረዋ  ብይኑን ሙሉ ለሙሉ አንባብያን እንድታነቡት ሲያቀርብላችሁ እራሳችሁ አንብባችሁ ግንዛቤ  እንድትወስዱ በማሰብ ነው። በተከበሩት ዳኛ ኤልዛቤት ሜየር የተጻፈው የብያኔ  ትችት እንደሚያስረዳው፣ ይግባኝ ባዮቹ ከሳሾች የቤተክርስቲያኑ የቦርድ አባላት አላግባብ ስልጣናቸውን ተጠቅመው መተዳዳሪያ  ደንቡን መቀየራቸው አግባብ አለመሆኑን ጠቅሰው መክሰሳቸውን ተነተርሶ የቀረበ  ክስ መሆኑን አስታውሶ ክሱ በመብት መደፈር አኳያና የቤተ ክርስቲያኑ ንብረት ይገባኛል ጥያቄ አንስቶ ቢሆን ኖሮ ፍርድ ቤቱ መግባትና መወሰን ይችል እንደነበር አውስቶ ነገር ግን በመተዳደሪያ  ደንቡ ላይ ብቻ ያተኮረ ስለሆነ ይህ ደግሞ በውስጥ መፈታት ያለበት እንጂ ፍርድ ቤት በእምነት ውስጥ ጣልቃ  መግባት የለበትም የሚል ብዙ ተመሳሳይ የቆዩ ውሳኔዎችን በመጥቀስ የበታች ፍርድ ቤት ቦርዱ የመተዳደሪያ  ደንቡን መቀየር ይችላል ብሎ  የበየነውን ውሳኔ አጽንቶ ወስኗል። የቤተክርስቲያን ቦርድ አባላት ክሱ በውሸት የተመሰረተ  የቦርድ አባላትን ስራ ለማስፈታት የተመሰረተ  መሆኑን የይግባኝ ፍርድ ቤቱ እንዲወስንላቸውና  ካሳ  እንዲጥልላቸው ያቀረቡትን ሳይቀበለው ቀርቷል።

ለምን ታዲያ የንብረት ይገባኛል ጥያቄውን ከመጀመሪያው አላነሳችሁም ብለን ያነጋገርናቸው ለጉዳዩ  ቅርበት ያላቸው ግለሰቦች የነገሩን ቢኖር ከመጀመሪያው ይህ  ሃሳብ ቀርቦ የከሳሾች ፍላጎት የቤተክርስቲያኑን አባላት መብት ለማስጠበቅ እንጂ ለመበታተን ስላልነበር ሃሳቡ ተነስቶ  ውድቅ እንደተደረገ ለመገንዘብ ችለናል።

ባሁኑ ሰዓት ግን የንብረት ይገባኛል ክስ ቢመሰረት ማንም ምእመን ሊቀበለው የሚችል ለመሆኑ በሂደት በቤተክርስቲያኑ አባላት ላይ የደረሰው በደልና  አሁን ቤተክርስቲያኑ ያለበትን  በማሰብ መናገር ይቻላል ብለው እንደሚያምኑም ለመረዳት ችለናል።

መረዋ  በእትምት ጅምሩ ላይ የጠቆማቸው ሁሉ ተራ  በተራ ተፈጻሚ ሆነዋል።

ካህናት ተባረዋል
አባላት ተበትነዋል
የስደት ሲኖዶስ ከበራፍ ቆሞ እየጠበቅ ነው
እምነት ሳይሆን ስልጣን፣ አባላት ሳይሆኑ ተመራጮች ፈላጭ ቆራጭ ሆነዋል።
የነበረው ገንዘብ መንምኗል፥
ፖለቲከኞች መሰባሰቢያ  ሲያገኙ አማንያን ከስብሰባ  ታግደዋል
በእምነት ሳይሆን በፖሊስ ለማስፈራራት ተሞክሯል
የቦርድ አባላት ወንጀል በይቅርታ  ሲታለፍ ግለሰቦች ወደፍርድ ቤት በመሄዳቸው ወይም ቦርዱ የሚደረገውን በመቃወማቸው ነፍሰገዳይ ዝሙተኛ ሌባ ሴሰኛ እየተባሉ ከእግዜር በተላከ ቁጣ የሞት ፍርድ ሳይቅር እንደተፈረደ  ሁሉ ተጽፏል።
በአባላት ላይ የክፍያ  ጫና  ተጥሏል።
በዘር እንዲከፋፈል ተደርጓል
የስደት ሲኖዶስ አባላት ሰፈር ተወለጆች እንዲጠናከሩ ሲደረግ ሌሎች በዘራቸው ተወንጅለዋል።
ሲፈርዱ የነበሩ ፈራጆች ዛሬ ተፈርዶባቸዋል።
የቤተክርስቲያን መስራቾች በመመስረታቸው ተነቅፈዋል ወዘተ

ልንል የፈለግነው ያላሰብነው አዲስ ክስተት አልተፈጠረም ለማለት ነው
ባጋጣሚ ትላንትና የደረሰን ዜና  ደግሞ  ወጣት የቤተክርስቲያን ልጆች ጥያቄ  አቀረባችሁ ተብለው መባረራቸውን መስማታችን ነው። ጥያቄው ምን ነበር ስንል
ለምን የረባ  ምሳ አትሰጡንም?
ገንዘብ የለንም ካላችሁ ለምን መብራትና ቴሌቪዥን ግዢ ሄዳችሁ?
በእኛ ስም ከበጎ አድራጊዎች የተገኘ ገንዘብ የት ገባ?
ሳንማር የምንመረቀው እንዴት ነው? የሚሉ እንደ ነበሩ ለመረዳት ችለናል።

እነዚህ  እዚህ የተወለዱና  ያደጉ ሕጻናት ደግሞ ፖለቲካውም አይገባቸው ውሸትም አይዋጥላቸው፥

መረዋ ላለፉት 5 ዓመት ከልባቸው ለእውነት ለፍትህ ለመብት ለታገሉ ምእመናን በሙሉ ያለውን አክብሮትና አድናቆት እየገለጸ ወደፊትም በዚህ መልክ ለሚነሱና ካሁን በኋላ  የንብረት ጥያቄ  ለሚያነሱ  ሁሉ ድጋፉን ለመለገስ ወደ ኋላ  እንደማይል ካሁኑ ቃል ይገባል።

የማንም መብት ሲጣሰ የግል መብት እንደተጣሰ  መቁጠር ትክክለኛ  ውሳኔ  ነው።

የሚሸነፍ ሰው ለመብቱ የማይነሳ ብቻ  ነው።

ሰላምና ፍቅር ለሁላችሁ ይሁን፥

የፍርድ ቤቱን ውሳኔ እንዳለ  ለማንበብ የምትፈልጉ ከዚህ በታች ያለውን በመጫን ያንብቡ

http://www.5thcoa.courts.state.tx.us/cgi-bin/as_web.exe?c05topin.ask+D+510527

Thursday, May 19, 2011

አትደግ ያለው ልጅ በእሳት ይጫወታል።

ወንድሞችና እህቶች እንደምን ከረማችሁ። ካነበባችሁን ውሎ አደረ። በየሳምንቱ በሬ  ወለደ ብለን መጻፍ አልለመደብንምና ወይንም እኛ ስንፈልግ እንጂ ከሌሎች ፉክክር በመግባት እንካ ስላንቲያ ማለት ባለመፍቀዳችን   ለናንተ የሚሆን ዜና አግኝተን እስክናዘጋጅ ድረስ ቆየን። ከወዲያኛው ጎራ የሴት ዘጋቢ የፍርድ ቤት ውሎ እንድትዘግብ ተለምና ከምትጓዝበት እንደቀረችና ፍርድ ቤት እንደዋለች ስናነብ ከምር ከልባችን ሳቅን። መሳቅ ብቻ አይደለም የቆየ የአለቃ ገብረሃናን ቀልድ አስታወሰን። ቀልዱ እንዲህ ነው። አለቃ ገብረሃና ከሸንጎ ላይ እንዳሉ አሽከራቸውን ይጠሩና በጆሮው ያችን ሴት ሂድና ማታ  አለቃ ይፈልጉሻል በልና  ጠይቀህ መልሱን ሰው እንዳይጠረጥር በወንድ ጾታ ቀይርና ንገረኝ ብለው ይልኩታል ሲመለስ ምን አለ? ብለው አሽከራቸውን ሲጠይቁት አሽከራቸው አልችልም ነፍሰ ጡር ነኝ ብሏል አለ ይባል ነበር። አባባሉ ፍርድ ቤት የነበረ ሴት አለማየታችንን ለመናገር ያክል ነው። የነበሩትን በመመልከት ደግሞ ጸሃፊዎቹን ማወቅ ብዙም የተወሳሰበ አልነበረም።

በእለቱ የከሳሽና  የተከሳሽ ጠበቆች ከዳኞቹ ለቀረበላቸው ጥያቄ  መልስ የሰጡ ሲሆን የከሳሽ ጠበቃ ክርክር አጭርና የማያሻማ ነበር። ይኽውም ክሱ የመብት እንጂ የኃይማኖት እንዳልሆነና ቦርዱ ካለ አባላት ፈቃድ በክርክር መሃከል ሕግ መቀየሩ አግባብ አይደለም የሚል ነው።

የቦርዱ ጠበቆች ክርክሩ የኃይማኖት መሆኑን በተለይም መሃበረ ቅዱሳን የተባለ  እምነት በመላው አሜሪካ እየረበሸን ነው ይህም የዳላስ ክስ የዛ ተቀጥላ ነው የሚል እረጅም ገለጻ ማድረጋቸውን ለመረዳት ችለናል። ጠበቆቹ ደግሞ ነገሮች በተራዘሙ ቁጥር ተጠቃሚዎች ናቸውና ለምን የቃል ክርክሩን መረጡ ማለት የዋህነት ነው። የከሳሾች ጠበቃ የቃል ክርክሩን ጊዜ ለመቆጠብና የጠበቃን ወጪ ለመቀነስ እንደማይፈልግ በይግባኝ ወረቀቱ ላይ መጥቀሱ ይታወሳል። የቦርዱ ጠበቆች ግን ገቢያችንን አትቀንስብንም እኛ እንፈልጋለን ብለው ቀጠሮው ተያዘ ክርክሩም ተደረገ። አሁን ዳኞቹ ምንም ይፍረዱ ምን ክርክሩ ይቀጥላል። ምን አልባትም የፌድራል ፍርድ ቤት ሊያየው የሚገባ  አቤቱታም እንደሚኖር ከምንጫችን የደረሰን ዜና ይጠቁማል። 

የሰው ስም ሲያጠፉ ግለሰብን ሲዘልፉ ቤተስብን ሲወነጅሉ የነበሩት የማዶ ጸሃፊዎች መከሰሳቸውን የሰማነው ከነሱ ብሎግ ላይ አልነበረም። በስድባቸው እንደሚቀጥሉና እንደማይፈሩ ያነበብነው ግን በብሎጋቸው ላይ ነው። እንደማይፈሩ እኛም እናውቃለን የሚፈራ ሰው ክፉና ደጉን የሚለይ ብሎም የሚመጣበትን ነገር አመዛዝኖ  የሚለይ ብቻ ነውና።  በፈንጂ የሚጫወት የማያውቅ ሰው ብቻ ነው ይባል የለ። 

ከሳምንት በፊት ቀደም ሲል በድንገት ከመከላችን በሞት የተለየች እህታችንን አርባ ለመደገስ የቤተክርስቲያኑን አዳራሽ $500 ከፍለው ሃዘንተኞቻቸውን የጋበዙት ቤተሰቦች በእለቱ ሊያሳዩት የነበረውን የሟችቷን የሕይወት ታሪክ ያዘለ የ 7 ደቂቃ ፊልም ለማሳየት የማሳያ ፕሮጀክተሩን በመልከላቸው ሲያዝኑ በአካል ታዝበናል። ቦርዱ አይቻልም ብሎ ሲነግራቸው ያዳመጡት ከሐዘንተኞቹ አንዱ ግለሰብ እኛ እኮ ቤተክርስቲያን አጥተን አይደለም እዚህ የመጣነው አልገባቸውም አሁን ግን እስከመጨረሻው አጡን ሲሉ አዳምጠናል። በመንፈሳዊ ጉዳይ ዘር ቦታ ሲኖረው ከማየት ይሰውረን ወንድሞችና እህቶች።  ይህንን የወሰኑት የቦርድ  አባላት የገደለ ጥይት ድምጹ ከሩቅ አይሰማም ብለው ከሆነ ተሳስተዋል። የግፍ  እንባ መጥፎ  መሆኑን ከመጽሐፍ እንረዳለንና። እዚህ ደግሞ ዜና ማሰራጫው ዘዴ ብዙ ነው። ካልሰማው ይልቅ የሰማው ብዙ ነው። ሰምቶ ምን አደረገ? ማለት ግን ትክክለኛ ጥያቄ  ነው።
ሌላው ዜና የቤተክርስቲያኑ የቦርድ አባላት ባለፈው ቅዳሜ አጠቃላይ የአባላት ስብሰባ ጠርተው እንደ ነበረ የሰማችሁት ጉዳይ ነው። በእለቱ ዙፋነ ወንበር የጨበጡ የመሰላቸው አዲስ ተመራጭ አቶ ሰሎሞን ከጎናቸው ከነበሩት ከአቶ ከተማ ጋር በመሆን።

አቶ  ሃይሉ እጅጉን   
ወይዘሮ ገነት ከበደን
ዲያቆን አርአያ  ኃይለመስቀልን ከስብሰባ  እንዳይገቡ መከልከላቸውን ስንሰማ  አዘንን። ለምን ቢሉ ቤተክርስቲያናችን መልሶ ከመሰባሰብ ወደ መፈራረስ መሄዱ ስለታየን ነው።አቶ ሰሎሞን አባራሪ አቶ ሃይሉ እጅጉ ተባራሪ ------- ወገኖቼ የሆነ ነገር የጎደለ  አይመስላችሁም።
አቶ ከተማ  ቤተኛ ዲያቆን አርአያ ባይተዋር -------- እግዚኦ ማለት አሁን መሰለን።
ወይዘሮ ገነት ተባራሪ ቀሪው አባራሪና አጋፋሪ------- ነገ  በኔ ማለት ይገባል።
የንብረት ጥያቄ  ቢመጣ እኮ ድርሻህን አሳየኝ ማለት እንደሚጀመር አንርሳ። የአቶ ኃይሉ እጅጉ በሺህ የሚቆጠር ችሮታ ቤተክርስቲያኑን እንደ ገነባው የምንጣላ  አይመስለንም። የአቶ  ከተማና የአቶ  ሰሎሞን ፉከራ  ግን  ቤተክርስቲያኑን  እያፈረሰው እንደሆነ አከራከሪያ ሆኗል። 
የዲያቆን አርአያ ለዚህ ቤተክርስቲያን ያበረከቱት አስተዋጽ ሁሉም የሚያውቀው ጉዳይ ነው። የአሁኑ የቦርድ አባላት ውሳኔ  ግን የቤተክርስቲያኑን ውድቀት እንደሚያጣድፈው እድሜ  ሰጥቶን የምንመለከተው ይሆናል።
የወይዘሮ ገነት ከበደ ለዚህ ቤተክርስቲያን ያደረጉትን እርዳታ ለማወቅ ምስክር ፍለጋ መሄድ የሚያስፈልግ አይመስለንም ። ምስክር የሚያስፈልገውስ የዛሬዎቹ ፍርድ ሰጪዎች አስተዋጽኦ ጉዳይ ነው። 

ግለሰቦቹ መዋጮ ሲከፍሉ እንቢ አልተባሉም። እምቢ የተባሉት ገብተው የሚያቀርቡት ጥያቄ ስላስፈራ ብቻ ነው።  የሕግ ሰዎች ይህንን
taxtion without reperesentation  ይሉታል።

ዛሬ የተባረሩትን አይተናል ነገ ደግሞ ሽማግሌ ነን ብለው የተቀመጡት አዛውንቶች ተራቸው ይደርሳል። ያኔ እነሱ ዛሬ ተነሰተው እንዳልቆሙ ሁሉ ለነሱም የሚቆም ይጠፋል። ትላንት ሕጉን ያጸደቁ ዛሬ ያሳለፉት ሕግ እነሱን እየጎዳቸው እያስተዋልን ነውና።

የድሮ ታሪክ ታስታውሳላችሁ ሁለት ሴቶች አንድ ሕጻን የእኔ ነው በማለት ተካሰው ቀርበው ዳኛው የማንኛችሁ እንደሆነ ማወቅ ስለማይቻል ሕጻኑ በቢለዋ ለሁለት ተሰንጥቆ ተካፈሉት ብለው ሲፈርዱ እናት ያልሆነችው በፍርዱ ስትስማማ እውነተኛዋ  እናት ግን እኔ ይቅርብኝ ሕጻኑን እሷ ትውሰደውና ታሳድገው  ያለችው። እኛም ያለውን ሁኔታ ስናስተውለው ከሳሾች ቤተክርስቲያኑን ለማዳን ቦርድ ነን ባዮች ደግሞ ፍርስርሱን ለማውጣት እየተጣደፉ ያለ ይመስለናል።

የቅዳሜው ስብሰባ  ምልዓተ ጉባኤው  አልሞላም ተብሎ  መበተኑን ስንታዘብ ሊቀመንበሩ አቶ  ሙሉጌታ  እንዳሉት ሁለተኛ ስብሰባ  በ 4  ይጠራና አሁንም በቂ ሰው ካልተገኘ በሕጉ መሰረት የቦርዱ ውሳኔ  ተፈጻሚነት ይኖረዋል። ብለዋል ይህ ደግሞ መጀመሪያ ሕጉን ቀየርን ሲሉ የተነሳውን  ተቃውሞ ያጠናክረዋል። ቦርዱ መተዳደሪያ ደንብ እንደ ፈለገው ከቀየረ፡ኮረም አልሞላም ብሎ  የ$10000 የእደሳ ባጀት ካጸደቀ፣ የማይፈልጋቸውን ማባረር ከቻለ አባል የሚኮነው ለምን ይሆን?

አንድ የገረመን ነገር ቢኖር የተባረሩትን ግለሰቦችና ያባራሪዎቹን የክርስትና እምነት ጥንካሬ ስናሰላስል የተሰማን ሃዘን ነው። እስቲ እያንዳንዳችሁ በግላችሁ ታዘቡ ፍርዱን እናንተው ለናንተው ስጡ።
 
ማን ነበር ተከራይና አከራይ እኩል ለቤቱ ጣራ አይጨነቁም ያለው? እየቆየ አባባሉ እየታወሰን  ተናጋሪው እየጠፋን ነው።
 
ይልቅስ አንድ የታወቀ ባንክ ዘራፊ ተይዞ ለምን ባንክ ዘረፍክ?ተብሎ ሲጠየቅ የመለሰውን እናስታውሳችሁና  እንሰናበታችሁ "ገንዘቡ ያለው እዛ ስለሆነ  ነው" ብሎ  ነበር። ቦርዱ የላከው 2009 የሂሳብ ሰንጠረዥ $ 75000 ለጠበቃ እንደዋጣ ያሳያል 2010 ስንት እንደሆነ አልነገሩንም ምናልባትም አይነግሩንም ይህ ገንዘብ የወጣው  እነ አቶ ሃይሉ እጅጉን ለማባረር፣ እናቶ ከተማን ለመሾም መሆኑ ነው። የፖለቲካ  ፍልሚያ  ነው ስንል ያልሰሙን ሰዎች ዛሬ እውነት አላችሁ ይሉናል ብለን እናምናለን።
 
በጉልበትና በፍርድ ቤት ፍቅር አይመሰረትም እውነትን የያዘ  ያለጥርጥር ያሸንፋል።

በእሳት የሚጫወት ግን አትደግ የተባለ ብቻ  ነው።

Wednesday, April 27, 2011

እሱ ከመቃብር ተነስቷል እኛስ?

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ። ለመጭው ዓመት በሰላም አቅፎ  ደግፎ  እንዲያደርስን እየጸለይን ሰላምና  ፍቅሩን እንዲያድለን አጥብቀን እንለምነዋለን።
መረዋ ከብዙ ዓመታት ጋብቻ በኋላ ልጆቻቸውን አስተምረው አስመርቀው የልፋታቸውን ውጤት እያስተዋሉ አሁንስ ለራሳችን እናስብ ብለው ባለፈው ቅዳሜ ሥጋወደሙ የተቀበሉትን የቤተክርስቲያናችን አንጋፋ ሽማግሌ የነበሩትንና የሚካኤል ቤተክርስቲያን የቦርድ አባል፡ የሽማግሌ  ኮሚቴ  አባል ሆነው ለዘመናት ያገለገሉን አቶ  ዳኜንና  ባለቤታቸውን እንኳን ደስ አላችሁ ሊል ይወዳል። በሚካኤል ቤተክርስቲያን የፋሲካ ዋዜማ  ቅዳሜ በመሃከላችን ባለመኖራቸው ያዘነው ብዙ እንደ ነበርን ለማወቅም ችለናል። ሐዘኑ የተፈጠረው ለምን ወደ ሌላ  ቤተክርስቲያን  ሄደው ሥጋወደሙ ተቀበሉ በማለት ሳይሆን ይህ እንዲሆን ምን ሚና ተጫወተን ይሆን? የሚለውን ወደኋላ መለስ በማለት የችግሮቹን ሂደት በመቃኘት ጭምር እንደሆነም ለማወቅ ችለናል። ስለሆነም የትም ቤተክርስቲያን ይሁን የት ዋናው የነሱ ምኞት መፈጸሙ ነውና መረዋ  በድጋሜ እንኳን ደስ ያላችሁ እያለ ለአቶ  ዳኘ ቤተሰብ በመላ ስሜቱን  ሲገልጽ ለደረሱበት መንፈሳዊ ድል ደግሞ መንፈሳዊ ቅናት እያደረበት ነው።

ከዚህ በፊት በነበረው እትምታችን ጠቅሰንላችሁ እንደነበረው ባለፈው ሳምንት በነበረው ቀጠሮ የከሳሽና  የተከሳሽ ጠበቆች የመከራረሪያ  ነጥባቸውንና የፍርድ ሃሳባቸውን አጠናቅረው ማቅረባቸውን ልንነግራችሁ እንወዳለን። የከሳሾች ጠበቃ ፋይሉን ያስገባው የስቅለት እለት ዓርብ እንደ ነበረ ስንረዳ ይህ ባጋጣሚ የሆነ  እንጂ ሆን ተብሎ የተደረገ  እንዳልነበረም ለማረጋገጥ ችለናል። ካሁን በኋላ ዳኛው ስሚዝ  ጉዳዩን እልባት ለመስጠት የግድ መወሰን ስላለባቸው በሳምንት ውስጥ ብይን ይሰጣሉ ብለን እንጠብቃለን። መረዋዎችም ውሳኔአቸው እንደደረሰን ለአንባብያን ለማቅረብ አሁንም ቃል እንገባለን።

በሚካኤል ቤተክርስቲያን በአቶ  ጸሐይ ጽድቅ ተገዝቶ ከ 5 ዓመት በላይ ሲያበራ የነበረው የቤተክርስቲያን መብራት እሳቸውን ለመጉዳት በሚል እንዲወርድ መደረጉን ስንሰማ  እጅጉን አዘንን። መብራቱን ለግሰው የነበሩት አቶ ጸሐይ ጽድቅ ቡራኬውን በወቅቱ የተቀበሉ ስለሆነ  ብሎም ለሚካኤል ካበረከቱ በኋላ  የሳቸው ንብረት ሊሆን እንደማይችል እየታወቀ ይህ መደረጉ ደግሞ የሚደንቅ ነው። የአቶ ሙላው ወራሽ ስጦታ የነበረው ቴሌቪዥንም እንደዚሁ ከደጀሰላም መነሳቱን ሰምተናል። የመብራቱን መነሳት ለመመስከር ስንችል የቴሌቪዥኑን መነሳት ግን ከመስማት ባሻገር መደረጉን ለማረጋገጥ ገና እድል እንዳላገኘን ልንገልጽላችሁ እንወዳለን። ያም ሆነ ይህ በቂም ላይ የተመረኮዘ ማናቸውም ውሳኔ ትክክል እንዳልሆነ ከመናገር ግን ወደ  ኋላ አንልም። በዚህ መንገድ ከተቀጠለ  ደግሞ ቦርዱ የማይወዳቸውን ግለሰቦች የመዋጮ ስጦታና የስለት ገንዘብ ከባንክ እያወጣ እንዳይበትነው እንሰጋለን ቢባል ትክክለኛ ጥርጣሬ ይመስለናል። የስደት ሲኖዶስ ለጊዜው ይቆይ የተባለው የምእመናንን ተቃውሞ  በመፍራት እንደሆነም መስማታችንን ስንነግራችሁ የመብት ትግል መቼም ይሁን በማ እየቀጠለ  እንደሚሄድ አሁንም ቃል እንገባላችኋለን። በሚመጣው ሳምንት ቀደም ባለው ጊዜ በወይዘሮ ጥሩዓየርና  በአቶ  ዳግም ተመስርቶ የነበረው ክስ ይግባኝ የቃላት ክርክር እንደሚኖር ባለፈው የጠቀስን በመሆኑ መደጋገም አስፈላጊ አልመሰለንም። ይህ የቤተክርስቲያን የመብት ጥያቄ  ክርክር ከተጀመረ ከሁለት ዓመት በላይ እየሆነ  ነው። ሳምንት ይቆያሉ ብለው ያላሰቡን የቦርድ ዓባላት በጥንካሬአችን መገረማቸውን እራሳቸው እየመሰከሩ ነው። ዛሬ መስራች አባላት በቦርዱ ውስጥ የሉም ዛሬ ትላንት የቦርድ አባላት ሆነው ሲወሰኑ የነበሩት እንደባይተዋር እየተባረሩ ነው ።  እንዳልወሰኑ እየተወሰነባቸው ወዳጅ እንዳልተባሉ ጠላትነታቸው እየተነገራቸው፡ ሕግ አስፈጻሚ እንዳልነበሩ ሕግ እየተፈጸመባቸው። ደንብ እንዳልጠቀሱ ደንብ እየተጠቀሰባቸው ነው።

ብዙዎች ከቤታቸው ገሚሶች ወደሌላ  ቤተክርስቲያን መበተናቸውን በደስታ  የሚመለከተው ቦርድ ጥቂት ሆነን ፈላጭ ቆራጭ ሆነን እንከርማለን ብለው አስበው ከሆነ አሁንም ተሳስተዋል እንላለን። ያላካበቱትን፡ ያልለፉበትን ገንዘብ መበተን፣ ያልሰበሰቡትን ምእመን አበሳጭቶ ማስኮረፍና  ከቤተክርስቲያን ማስቀረት ቀለላል ሊሆን ይችላል መገንባት ግን የዘመናት የሥራ  ውጤት መሆኑን መረዳት ቢችሉ ግን ትልቅነት ይመስለናል። ኩርፊያ  ያለበት ቤተመቅደስ ደግሞ ቁጣን እንጂ ሰላምን ያመጣል ማለት አይቻልም። ምእመናንን  ብቻ  ሳይሆን ካህናትንም የሚከለክል ደግሞ ትልቅ ድክመት ያለው ነው እንላለን።
 እሱ ከመቃብር እንደተነሳ  እኛስ ብለን ብንጠይቅ መልካም ነው።
ቸር ወሬ  ያሰማን

Wednesday, March 23, 2011

የዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ

እንደምን ከረማችሁ ምእመናን

የተለየ ነገር ሳይኖር በተደጋጋሚ እናደርገው እንደ ነበረው በተከታታይ ባለመውጣታችን ምን ነካችሁ?  ላላችሁን። መረዋን አትግደሉብን ብላችሁ ለጠየቃችሁን። መረዋ ላይ ካልወጣ እውነት አይደለም ላላችሁና እምነት ለጣላችሁብን ሁሉ ምስጋናችን ወሰን የለውም። ዋሽተን ከምንከበር ይልቅ እውነቱን ተናግረን ብንወገር እንደምንመርጥ መናገር ደግሞ እውነትነቱ አንደማያጠራጥር ምስክሮቻችን እናንተ  ናችሁ።  በመሆኑም እንደ ተለመደው የዛሬን  የፍርድ ቤት   ውሎ እናካፍላችሁ። 

ባለፈው እትምታችን እንደ ነገርናችሁ  የዛሬው ቀጠሮ በ 192 የካውንቲ ችሎት በዳኛ ስሚዝ ፊት የተደረገ ክርከር ነበር። ባለፈው እረዳት ዳኛ የቦርዱ ሹማምንት ከከሳሾች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን የመመለስ ብሎም የቤተክርስቲያኑን ዶሴዎች የማሳየት ግዴታ አለባችሁ ብለው የወሰኑትን ውሳኔ በመቃወም የቦርዶቹ ጠበቃ  ለዋናው ዳኛ ስሚዝ ይግባኝ ማለታቸው ይታወሳል። የዛሬው ቀጠሮ ከመድረሱ በፊት ባለፈው በቦርዱ ላይ ተጥሎ የነበረውን እገዳ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እንዳነሳላቸው የዘገብነው ጉዳይ ነው።

በዛሬው  እለት የተከሳሾች ጠበቃ ለፍርድ ቤቱ በ march 21st ያስገቡት  ማመልከቻ ለከሳሾች ጠበቃ እንዳልደረሳቸው ለፍርድ  ቤቱ ሲናገሩ ፍርድ ቤቱ ለምን? ብሎ  የተከሳሾችን ጠበቃ  ሲጠይቅ መልሳቸው በfax ልከናል የሚል  ነበር። ፋክስም እንዳልደረሳቸው የተናገሩት የከሳሾች ጠበቃ ባላዩት ማመልከቻ  ላይ ምንም ውሳኔ  ሊሰጥ  እንደማይቻል ተናግረው ዳኛው ተስማምተዋል። ዳኛው የይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት በሃይማኖት ጣልቃ  አትግቡ ብሏልና ለምን ጉዳዩን አየዋለሁ? ብለው ለጠየቁት ጥያቄ የተከሳሾች ጠበቃ  እኛም የምንለው እሱን ነው ብለው ሲመልሱ፣ የከሳሾች ጠበቅ ግን የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የወሰነው በእገዳው ላይ እንጂ በክሱ ይዘት ላይ አይደለም በማለት ተከረክረው ለዚህም በውሳኔው መደምደሚያ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን 
ፍሬ ሃሳብ ሳይተችበት ለዳኛ ስሚዝ ማስተላለፉን ጠቅሰዋል። የከሳሾች ጠበቃ  አያይዘውም አሁንም ቢሆን በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ አልስማማም ያ  እንዳለ  ሆኖ ለክቡር ፍርድ ቤቱ ልጠይቅ የምፈልገው እነዚህ የቦርድ አባላት እንደ ፈለጉ ሕግ መቀየር ከቻሉ ነገ  አዲስ ሕግ አውጥተው ንብረቱን ወስደው ቤተክርስቲያኑን ሸጠው ወደ ጃማይካ  ቢሄዱ ምን የሚያግዳቸው ነገር አለ። እዚህ ቤተክርስቲያን አባል መሆን ለምን ያስፈልጋል?  ፈላጭ ቆራጩ ቦርድ እንጂ አባላት ምንም መብት የላቸውም። የከሰሰ  ከአባልነት ይባረራል ካሉ። አባል ለመሆን ማመልከቻ  አስገብቶ  የቦርዱን ፈቃድ መጠየቅ ካለበት ስልጣኑ የምእመናን ሳይሆን የቦርዱ ነው ብለዋል። ስለሆነም ቦርዱ ነገ  ሕጉን  ቀይሮ ምንም ማድረግ ይችላል አባል ምንም መብት የለውም ብለው ለፍርድ ቤቱ አሳስበዋል። በተጨማሪም ይህ ቤተክርስቲያን የ  501 C ፈቃድ ያለው እስከ ሆነ ድረስ  የፌድራልና የስቴት ሕግ የመከተል ግዴታ  አለበት በሃይማኖት ሽፋን ወንጀል መስራት አይችሉም ብለዋል። የተከሰሱት የቦርድ አባላት የራሳቸውን ሕግ እንኳን የማያከብሩ ናቸው ለዚህም የምርጫቸውን ሁኔታ መመልከት ይቻላል በማለት ተከራክረዋል። የተከሳሾች ጠበቃ የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ከወሰነው ውጭ ፍርድ ቤቱ ምንም ማድረግ አይችልም ብለው ዛሬውኑ ክሱ ተሰርዞልን እንሰናበት ብለው ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ነበር።

በመጨረሻም ዳኛው ሁለቱ ጠበቆች ተስማምተው የመከራከሪያና  የፍርድ ሃሳባቸውን ከዚህ በፊት ከነበሩ ተመሳሳይ  የተለያዩ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ጋር እንዲያቀርቡላቸው ሁለት ሳምንት ሲሰጡ ስምምነቱን አስመልክቶ የተከሳሽ ጠበቃ ጽፈውና ፈርመው ለከሳች ጠበቃ እንዲያሳልፉ የከሳሽ ጠበቃ ደግሞ ፈርመው ለፍርድ ቤቱ እንዲያቀረቡ ነግረዋቸዋል።

ዳኛው የሁለቱን መከራከሪያ ነጥብና የፍርድ ሃሳብ ካዩ በኋላ ማስረጃ መስማት እንደሚያስፈልግም ሆነ ክርክሩን ለመክፈት ወይንም ለመዝጋት ውሳኔ  ለመስጠት ለ APRIL 15 ቀጠሮ  ሰጥተው የእለቱ ችሎት  ተፈጽሟል።

በተጨማሪም በወይዘሮ ጥሩአየር እና  በአቶ  ዳግም ከሳሽነት ተመስርቶ በዳኛ  እስሚዝ የቦርዱ አባላት ካለ አባላት ፈቃድ ሕጉን መቀየር ይችላሉ ብለው የበየኑት ብያኔ  የሚታወስ ነው። ውሳኔውን በመቃወም ከሳሾቹ ለይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ይግባኝ  ማለታቸው ይታወሳል። ስለሆነም ጉዳዩን በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እያለ ከሳሾች ፍርድ ቤቱ ያለውን መረጃ ተመልክቶ  ውሳኔ  ይስጠን ቢሉም የቦርዱ ጠበቆች የለም የቃል ክርክር እንፈልጋለን በማለታቸው የቃል ክርክሩን ለማዳመጥ ጉዳዩ ለመጭው MAY 4, 2011 
ሰዓት 1:00PM  
ላይ መቀጠሩን ልንነግራችሁ እንወዳለን።
ቦታው 600 COMMERCE # 200
COURT OF APILE
FIFTH DISTRICT OF TEXAS


ማንኛውም የቤተክርስቲያን ምእመን በፍርድ ቤት በመገኘት ክርክሩን ማዳመጥ  እንደሚችል ስንነግራችሁ በደሰታ  ነው።
የቦርድ አባላት የማያልቅ ገንዘብ ስላላቸው ብዙ የማቆያ ዘዴዎችን እንደሚጠቀሙ ትላንት ፍርድ ቤት የተነገረ ሲሆን፣ መብታቸው የተደፈረው ምእመናን ደግሞ  ፈጣሪንና ደጋፊዎቻቸውን ይዘው መታገላቸውን እንደማያቆሙ ከሂደቱ መገንዘብ ይቻላል።

መረዋ ለምእመናን የሚጠይቀው ነገር ቢኖር መብት የሌለው አባልነት ምንድነው? የሚል ይሆናል።

መረዋም የዛሬውን ዘገባ  በዚሁ ያበቃል።

Friday, March 4, 2011

ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሰጠ

ውድ አንባብያን እንደምን ከረማችሁ

ባለፈው የቦርድ አባላት ግለሰቦችን ከቤተክርስቲያን እንዳያባርሩ ዶሴዎችን እንዳያጠፉ ተጥሎባቸው የነበረውን እገዳ በመቃወም ይግባኝ  ማለታቸው የሚታወስ ነው። በትላንትናው እለት ጉዳዩን የሰማው ፍርድ ቤት ዳኛው አስቀምጦት የነበረውን እገዳ  በማንሳት ክርክሩን ወደሚያዳምጡት ዳኛ መልሶ  መላኩን ለመረዳት ችለናል።   

በዳኞቹ አባባል የመታደደሪያ  ደንቡ ማንንም ሰው ቤተክርስቲያን እንዳይመጣ ቁርባን እንዳይቀበል ቦርዱ መከልከል አይችልም የሚለውን ይህ በውሰጥ ሊፈታ የሚችል በመሆኑ ፍርድ ቤት ማዘዝ አይችልም ብለው  ሲወስኑ የጉዳዩን ጭብጥ ክርክር ግን አናይም በማለት ውሳኔው እገዳውን በተመለከት ላይ ብቻ ያተኮረ መሆኑን ጠቅሰው ሁኔታውን እንዲያዩትና ክርክሩን እንዲሰሙ ለዳኛ ስሚዝ ዶሴውን መልሰው መላካቸውን ጠቅሰዋል።

ገንዘብ እንዳያባክኑ  ዶሴዎችን እንዳያጠፉ ተጥሎ  የነበረውን እገዳ ዳኞቹ ቦርዱ ገንዘብ ለማባከኑና  ዶሴዎችን ለማጥፋቱ የቀረበ  መረጃ ባለመኖሩ እገዳውን አንስተንዋል ሲሉ  ወደፊት ግን ይህ ለመደረጉ መረጃ  መስማት እንዲችሉ ለዳኛ ስሚዝ ጉዳዩን ክፍት በማድረግ ትተውታል።

ይህንን  አስመልክቶ  ሊቀርብ የሚችል ብዙ መረጃ  መኖሩን ስለምናውቅ የሚያስጨንቅ አለመሆኑን ለአንባብያን መናገር እንወዳለን። እስካሁን ምንም ክርክር ሳይጀመር ምስክር መስማት ሳይቻል  በአሰራር ብቻ  እየተወሰነ  ያለውን ጉዳይ አለቀ የሚሉ ካሉ ትልቅ ስህተተ  እየተሳሳቱ እንደሆነም መናገር እውነት ይሆናል።

የይግባኝ ፍርድ ቤቱ በእገዳው ላይ ብቻ ውሳኔ መስጠታቸውን ተናግረው ክሱን አስመልክቶ ምንም ውሳኔ አለመስጠታቸውን አስፍረዋል። ይህንን  ማድረግ የሚችሉት ዳኛ ስሚዝ እንደሆኑም ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።  ለዚህም ነው ዶሴው ወደሳቸው ፍርድ ቤቱ የተመለሰው።

በ3/23/2011 9:15 AM

በዳኛ ስሚዝ ችሎት እንድንገናኝ ጥሪ እያቀረብን  ለዛሬው በዚሁ እንሰናበታችኋለን።

ክርክሩ ተጀመረ  እንጂ አላለቀም። 

Tuesday, February 22, 2011

የፍርድ ቤቱ ቀጠሮ

ውድ አንባብያን እንዴት ከረማች? እኛ አሁንም የጀመርነውን ለመጨረስ ከመታገል ወደ ኋላ አላልንም። የተፈጠረ ብዙ ነገር ብንታዘብም የፍርድ ቤት ዜና ከማግኘታችን በፊት ለእትምት ላለመውጣት ወስነን ነበርና ይህንኑ ስንጠብቅ ሰነበትን። እነሆኝ በዛሬው እለት የደረሰን ዜና እንደሚጠቁመው ባለፈው ተላልፎ  የነበረው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ለ March 23, 2011 9:30 AM መቀጠሩንና ሁላችሁም መጋበዛችሁን መረዋ ማሳሰብ ይወዳል። ስለሆነም በተባለው ቀን ፍርድ ቤት ለመገኘት ካሁኑ የስራ እቅዳችሁን  እንድታስተካክሉ በድጋሜ  እናሳስባችኋለን። 

በተጨማሪ ከማንም ያልወገነ ገለልተኛ የተባለው ቤተክርስቲያናችን የአመራር አባላትና ካህናት ባለፈው ሳምንት ወደ ሂውስተን በመጓዝ ከስደት ሲኖዶስ አባቶች ጋር መገናኘታቸውን የደረሰን ዜና  ይጠቁማል። በወቅቱ በስፍራው  ተገኝተው የነበሩት አባ መልከጸዴቅ የዳላስ ሚካኤልን ወደ ስደት ሲኖዶስ መጥቶ  የቤተክርስቲያኑ አመራሮ ች በመሃከል መገኘታቸውን ከማብሰራቸውም በላይ ከዚህ በፊትም 7 ዲያቆናትን የስደቱ ሲኖዶስ ድቁና  መስጠቱን አውስተዋል። በመቀጠልም ከኮሎምቦስ የስደት ሲኖዶሱ ካህን ወደ  ዳላስ ተልከው በስራ  ላይ እንደሆኑም መጠቆማቸውን የደረሰን ዜና  ያረጋግጣል። የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ዘማርያንም የቤተክርስቲያኑን አልባሰ መዘምራን አጥልቀው ይዘምሩ እንደነበርም ለማረጋገጥ  ችለናል።

ገለልተኛ የተባለው ይህ ቤተክርስቲያናችን ማንንም ሲኖዶስ አንደግፍም ሲባል ቆይቶ ዛሬ የቦርድ አባላት በእንግድነት ከነባለቦቶቻቸው መገኘት ብቻ  አይደለም መዘመር ከቻሉ ገለልታኛነቱ እምኑ ላይ እንደሆነ እራሳችሁ እንድትጠይቁ ለናንተ  እያቀረብን መረዋ  ከዓመት በፊት ያነሳው የቦርድ አባላት እቅድ እየተፈጸመ  መሆኑን ከመታዘብ በስተቀር አልተደነቅንም። ትላንትናም ሆነ  ዛሬ ትግሉ ቤተክርስቲያኑን ተቆጣጥሮ የፖለቲካ ዓላማ  መጠቀሚያ ለማድረግ እንደሆነ የምናውቀው ነገር ፣ የተናገርነው ነገር ነበር። ትላንት ውሸት ተብለን ነበር ዛሬ  ምን እንባል ይሆን?

የወር ሰው ይበለን?

የመብት ትግላችን ይቀጥላል።

Wednesday, February 9, 2011

ዘግይቶ የደረሰን

እንዴት ሰነበታችሁ ውድ አንባብያን

ባለፈው እትምታችን እንደነገርናችሁ ተከሳሽ የሆኑት የቤተክርስቲያኑ የቦርድ ባለስልጣናት ቀደም ባለው ዳኛ ተወስኖ የነበረውን

በመቅደስ ውስጥ ፖሊስ አታስገቡ
አማንያንን አታባሩ
መዛግብቶችንና የኮሚፒውተር መረጃዎችን እንዳታጠፉ ብሎ የወሰነባቸውን በመቃወም ይግባኝ  ማለታቸው የሚታወስ ነው። በመሆኑም በ2 / 7/ 2011 ያስቻለው የይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት በከሳሽና  በተከሳሾች ጠበቆች የቀረበውን የቃል ክርክር አዳምጠዋል። በወቅቱ የተሰየሙት 3 ዳኞችም ለሁለቱም ጠበቆች  እንዲብራራላቸው የፈለጉትን ጥያቄዎችም ጠይቀው መልሱን  አዳምጣዋል።

ከሳሾችን አናውቃቸውም ያሉት የተከሳሾች ጠበቃ ከሳሾች ማክዶናልድ  ምግብ ቤት ሃምበርገር ተመላልሰው በመበላታቸው የማክዶናል የቦርድ አሰራር አላማረንምና የመቀየር መብት አለን እንደሚል ግለሰብ ናቸው ብለዋል። ስለሆነም እኛም ያልመሰለንን  የማስዋጣት የማባረር መብታችን መጠበቅ አለበት ምክንያቱም ቤተክርስቲያን በመሆናችን  መንግስት ጣልቃ  ሊገባብን አይችልም መንግስት መግባት የሚችለው የንብረት ይገባኛል ጥያቄ ይዘው ቢቀርቡ ነበር  ማለታቸውን ለመረዳት ችለናል።
የከሳሾች ጠበቃ በበኩላቸው እነዚህ ተመራጮች ያላግባብ የተመረጡ ከመሆናቸውም በላይ ጥያቄ ተጠየቅን ብለው ሴትና ሕጻናት በተሰበሰቡበት ወገን ፖሊስ እያስገቡ ያሳሰሩ ብሎም መብታቸውን በመጠቀም አባላትን ለማባረር የተነሱ መሆ ናቸውን አውስተው ጉዳዩ የእምነት ሳይሆን የመብት መገፈፍ መሆኑን አስረድተዋል። በ2/10/2011 ዳኛ ስሚዝ በይግባኝ ሰሚነት የሚያዩት ለውሳኔ  የቀረበ  መዝገብ እንዲያሳዩ  በበታች ዳኛ  የተወሰነውን አሻፈረን በማለት አሁንም የቦርዶቹ ጠበቃ ያቀረበው ስለለ የእሱንም ውጤት የይግባኝ  ሰሚው ፍርድ ቤት መጠበቅ ይኖ ርበታል ብለዋል።
ፍርድ ቤቱ የቀኑን የጠበቆች ገላጻ አዳምጦ የእለቱ ሸንጎ ፍጻሜ  ሆኖ ተበትኗል።




ዘግይቶ  የደረሰን ዜና በነገው እለት 2/10/2011 ተቀጥሮ  የነበረው ይህ ቀጠሮ በከሳሾች ጠበቃና በዳኛው የፕሮግራም መጋጨት መተላለፉን ለመረዳት ችለናል።  የቀጠሮውን ቀን እንደደረሰን ለአንባብያን እናስታውቃለን።

የከርሞ  ሰው ይበለን። 

 

Monday, January 24, 2011

በትላንትናው ቀን የተጠራው ስብሰባ በሙሉ መግባባት ተፈጸመ።

ባለፈው እንደ ነገርናችሁ በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍተሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በትላንትናው እለት ጠርቶት የነበረው ስብሰባ በመግባባትና በሙሉ ስምምነት መገባደዱን የደረሰን ዜና አስታውቋል። በወቅቱ በተደረገው ስብሰባ  የተገኙት እንግዶች ከምሳ ግብዣው በኋላ ሰፊ ውይይት እንዳደረጉ ሲነገር፣ በወቅቱ የአራቱም የኮሚቴው ተወካዮች በየተራ  ለተሰብሳቢው ስለተደረገው ያለፈ የኮሚቴ የስራ ክንውን መግለጫ መሰጠታቸውንም ለመረዳት ችለናል። በዜናችን መሰረት የመንፈሳዊ ኮሚቴ አባላት ከቤተክርስቲያናችን እየተገፉ የሚገኙትን አባላት መንፈሳዊ ጽናታቸን ለማጠናከር በዓርብ ምሽት የሚደረጉትን ትምህርቶች በየሰዎስት ወሩ የተዘጋጁትን የመንፈሳዊ ጉባኤዎች በሚያስደንቅ መልኩ ማካሄድ እንደቻሉ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ይህንንም ማድረግ የተቻለው ዓርብ ማታ በሚደረገው መንፈሳዊ ትምህርት ተካፋዮች ጉልበትና ከኪስ በተዋጣ ወጭ እንደ ሆነም የኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ተናግረዋል። በወቅቱ ኮሚቴውን በማሰባሰብና በማስተማር በመምራት ያገለገሉት ከቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በሌሊት በፖሊስ ተከበው የመሰናበቻ ወረቀቱን እንዲፈርሙ የተገደዱትና፡ ከቤተክርስቲያኑ ቦርድ ለኢሚግሬሽን በተጻፈ  ደብዳቤ  የኢምግሬሽናቸው ሁኔታ እንዲታገድና ከአገር ከነቤተሰባቸው እንዲባረሩ የተጠየቀባቸው መላከ ሳህል አወቀ ሲደልል እንደ ነበሩ ለተሰብሳቢዎቹ ተናግረዋል። በአሁኑ ሰዓት መላከ ሳህል አወቀ አትላንታ የሚገኝ ደብር ቀጥሯቸው ወደ አትላንታ መሄዳቸውም ለተሰብሳቢው ተገልጿል። ስለሆነም ቀደም ብለው ወደ አዲሱ ሥራቸው የተዛወሩት መላከ ሳህል አወቀ የዳላስን ምእመናንን ለመጨረሻ ጊዜ ለመሰናበት በፊታችን ዓርብ 1/28/2011ዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ባሻገር በሚገኘው የኬንያውያን ቤተክርስቲያን አዳራሽ ውስጥ እንደሚገኙ ሲነገር፡ ማንኛውም ምእመን ቤተሰባቸውንና እሳቸውን ለመሰናበት በዚሁ እለት እንዲገኝ ኮሚቴው ለሁሉም የዳላስ ምእመን ጥሪውን አቅርቧል። በዚህ አጋጣሚ መረዋ ለኝህ ቆራጥ ካህን ያለውን አድናቆትና ያላቸውን ቆራጥነት እያደነቀ፤ መጭው የሥራ ቦታቸው የተቃና እንዲሆን ምኞቱን ይገልጻል። መላከ ሳህል አወቀ እንደ አባት የሚርቁብን ቢሆንም ምሳሌነታቸው ግን ከልባችን ለዘላለም ይኖራል። የመንፈስ አባቶ ችን ስናነሳም እንደ ምሳሌ የምንጠቅሳቸው ይሆናሉ። ለቤተሰቦቻቸው ያለንንም አድናቆት ስንገልጽ በደስታ ነው። በተለይ ለውድ ባለቤታቸው መረዋ ያለውን አክብሮትና የመንፈሰ ጠንካራነት አርአያ መሆናቸውን መመልከቱን ሲጠቅስ በኩራት ነው።

የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ተዋካይ ደግሞ በተለያየ መንገድ ለአባላት የተላኩ መልእክቶች እንዲዳረሱ ማድረጉን በመናገር የኮሚቴው ልሳን የሆነው WWW.MELEKET4U.BLOGSPOT.COM ከመቼውም በበለጠ ከዚህ በፊት የተደረጉትንም ሆነ ወደፊት የሚደረጉትን ለአባላት ለማስነበብ በገጹ ላይ እንደሚለጥፍ ቃል ከመግባቱ ባሻገር ከብሎግ አልፎ WEB PAGE ወደፊት ለማውጣት እቅድ ላይ መሆኑን ተናግሯል።

የአባላት ኮሚቴ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት የደጋፊዎቻችን ቁጥር ከ200በላይ እንደሆነ  በመጠቆም አሁንም ከሌላው ወገን የሚሰነዘረውን የውሸት ወሬና ስድብ በተቋቋምን ቁጥር ካስተዋልኩት ደጋፊዎቻችን እየበዙ መሄዱን አውቃለሁ በማለት ጠቁመዋል። ለዚህም ዋናው መሳሪያችን ሲሳደቡ አለመሳደባችን፣ አለመዋሸታችን፣ ስንጀምር ያነሳነው የመብት ጥያቄ አሁንም በእንጥልጥል መሆኑና አለመዋዠቃችን  እንደሆነ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል።

የሕግ ኮሚቴ ተወካይ በበኩላቸው ቤተክርስቲያን እንዴት ይከሰሳል የሚሉት ግለሰቦች ለምን የአባላት መብት ይደፈራል? ሲሉ ያለመሰማታቸውን ተናግረው፡ ለመብት እንቆማለን ያለ ማንም ግለሰብ መብቱ ሲጣስ ያለው አማራጭ በጉልበት መጠቀም ሳይሆን በሕግ መከላከል ብቻ ነው፥ ብለው የሚገርመው ቤተክርስቲያንችን ተከሰሰ  ያሉት የቦርድ  አባላት ባዲስ መልክ እንደ መከላከያ ያመጡት ነጥብ ቢኖር በቦርድ አባልነታችን በግል መከሰስ የለብንም ቢፈልጉ ከሳሾች ቤተክርስቲያኑን ይክሰሱ ብለው ፍርድ ቤቱን መጠየቃቸው እንዳስገረማቸው ተናግረዋል። ሆኖም ከትላንትናው በተሻለ ሁኔታ ጉዳዩ እየተፋጠነ መሆኑን አብራርተው ስለፍርድ ቤቱ ሁኔታ አጭር ገለጻ አድርገዋል፡፡

በገለጻቸው መሰረት ከዚህ በፊት ዳኛው  ምእመንን ከቤተክርስቲያን አትከልከሉ። ፖሊስ ወደ መቅደስ አታስገቡ። ዶሴዎችና ማናቸውንም መረጃዎች አታጥፉ ብለው ያዘዙትን  ትእዛዝ አንስማማም በማለትምእመንን የማባረር መብት አለን፣ ፖሊስ በመቅደስ ውስጥ  ማስገባት አለብን፣ ዶሴዎችንና ማናቸውንም መረጃዎች እንድናጠፋ ይፈቀድልን፣ ብለው ይግባኝ ባሉት መሰረት በ 2/7/2011 3:00PM ላይ በ ይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት 3 ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የከሳሽና የተከሳሽ ጠበቆች 30 ፤ 30 ደቂቃ ተሰጥቷቸው ክርክር ስለሚያደርጉ ማንኛውም ሰው፥
600 COMMERCE DALLAS COUNTY COURT BUILDING 2nd FLOOR በመገኘት ማዳመጥ  እንደሚችል ተናግረዋል።

በተጨማሪ በ 2/10/2011 192court በመገኘት ባለፈው እረዳት ዳኛ በቦርዱ ላይ የፈረዱባቸውን የከሳሾችን ጥያቄዎች እንዲመልሱ የታዘዙትን ቦርዱ አሻፈረኝ ብሎ  ይግባኝ ባለው መሰረት ዳኛ ስሚዝ ፊት ቀርበው የሁለቱም ጠበቆች እንደሚከራከሩ ስንነግራችሁ አሁንም የምትችሉ ሁሉ ከላይ ባለው አድራሻ በ 9:00 AM በመገኘት እንድታዳምጡ ብለው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። አያይዘውም ዳኛው በዚህ ጉዳይ ላይ የሚሰጡት ብይን ይግባኝ የሌለውና የመጨረሻ  መሆኑንም ለተሰብሳቢዎቹ ተናግረዋል።

በመደምደሚያው የስብሰባው ሰብሳቢ፣ ሁሉም ላደረጉት እርዳታ ከልብ መነካታቸውን ተናግረው ለመብት አለመቆም በራሱ ድክመት መሆኑን  ተናግረዋል። በተለያየ  መንገድ እርዳታ የሚያደርጉትን ግለሰቦች አመስግነው አሁንም እርዳታው እንዲቀጥል አሳስበዋል።

መረዋ ሁላችሁንም በተባሉት የፍርድ ቤት ቀጠሮዎች እንድትገኙ  ጥሪውን እያስተላለፈ ለዛሬው በዚሁ እንሰናበታችኋለን።

የሳምንት ሰው ይበለን።

Friday, January 14, 2011

የተናገርነው እየተፈጸመ በመሆኑ ትንቢተኞች ነን አላልንም።

ሰላምና  ፍቅር ለሁላችሁ ይሁን አንባብያን እንዴት ከረማችሁ።

አንድ ነገር ዛሬ ደጋግመን ደጋግመን መናገር የምንወደው ነገር አለ። መረዋ እንደ ጦማር መውጣት ከጀመረበት ሰዓት ጊዜ  ጀምሮ የዋሸነውና አንባቢዎቻችንን ያደናገርንበት ጊዜ የለም። ከጅምሩ ስንለው የነበረው ነገር በሙሉ እየተፈጸመ ስናይ ደግሞ ትንቢተኞች ነን ብለን አልተመጻደቅንም። እትምት ላይ የምናመጣውን ማናቸውንም ነገር ግራና ቀኝ ሳናገናዝብ ጽፈን አናውቅም። አጀማመራችን ለጉራ ሳይሆን ባለፈው እንዳልነው መረዋ ሞተ የምንለው ውሸት ይዞ የተነሳ እለት ነው ብለን ስለምናምን መጠንቀቃችንን ለናንተ ለማረጋገጥ ነው። ዛሬ የተለየ ዜና ይዘንላችሁ አልቀረብንም። ስትሰሙት የከረማችሁትን እንጂ። ባለፈው ሳምንት ከእትምት እንድንቆጠብ በተጠየቅነው መሰረት ቃላችንን ፈጽመናል። ያን ስናደርግ ደግሞ ለውጥ ይመጣል ብለን አስበን እንዳልነበረ ልታውቁልን ይገባል። ያ የገባንው ቃለ  ቀጠሮ  ሲያከትም እነሆ እትምታችንን ጀምረናል።

ሰሞኑን ምርጫ ለማካሄድ የቦርድ ተመራጮች ደፋ ቀና እያሉ ነው። የፖለቲካ ድርጅቶችም ይወክሉናል የሚሏቸውን ለምርጫ አሰልፈዋል። እነማን እንደሆኑ ደግሞ ያነበባችሁትና የሰማችሁት ጉዳይ ነው።አዲሶች ተመራጮች ሆነው የቀረቡት ግለሰቦች ትልቅ ሹመት የሚያገኙ መስሏቸው ተነስተው ከሆነ ትልቅ ስህተት እየተሳሳቱ ነው። እየነደደ  ባለ ቤት ነዳጅ ይዞ  መግባት እሳቱን ማፋጠን እንጂ የሚያጠፋው አይሆንም። መቃጠሉ ይሻላል የሚሉ ከሆነ ሹመት ያዳብር እንላቸዋለን።

ምርጫውን ለማስቆም ከ 60 በላይ የሚሆኑ የቤተክርስቲያኑ አባላት በፊርማ ቦርዱን እንደጠየቁም ሰምተናል። ምላሹ ምን ይሆን? ብለው የጠበቁ ካሉ አናውቅም እንጂ እኛ እንቢ እንደሚሏቸው እርግጠኞች ነበርን። እንዳልነውም የቦርዱ አባላት የተሰጣቸውን ፊርማ ወርውረው ምክንያት እየፈጠሩ ምርጫውን ማስቆም የሚችል ምንም ሃይል አይኖርም ማለታቸውን ሰምተናል። የፈራሚዎቹ አባላት ሌላ የምንጠይቀው አለን እኛ በእግዚአብሄር ቤት ተስፋ አንቆርጥም ማለታቸውንም ከተጨባጭ ምንጮች የደረሰን ዜና አብስሮናል። ሚካኤል ይርዳቸው እንላለን። እኛ ግን መብትን ማስከበር የሚቻለው በሕግ ብቻ  እንደሆነ  ከተቀበልን ቆይተናልና ከሕግ ወጪ ለውጥ እንደማይመጣ ከተገነዘብን ውሎ  አደረ። ለዚህም ነው መረዋ ክስ የመሰረቱት ግለሰቦች የመክሰስ ሱስ ይዞአቸው ሳይሆን መፈናፈኛና አማራጭ አጥተው ነው በማለት ከሳሶችን ደግፎ  የተነሳው።

ከሳሾች አባል አይደሉም ያሉ የቦርድ ተመራጮች አባል ያልሆኑትን ለቦርድ እጩ አድርገው እያቀረቡ ነው።
የአባላትን ቁጥር ለማብዛት ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አባላትን እየተዋሱ እንደሆነም እየተመለከትን ነው።
የጊዮርጊስ አስመራጭ ኮሚቴ አባል የሚካኤል እጩ የሆኑት ባለቤታቸው ጊዮርጊስ ስላልተመረጡ ተናደው ነው ሲባል አልሳቅንም ቀልዳችሁን ነው አልን እንጂ።  
በኮሚቴ አባልነት ያላገለገሉ ተመራጭ ሆነው ሲቀርቡ ምነው?  አላልንም የምናውቀውን አጠናከረልን እንጂ። የራሳችን መተዳደሪያ ሕግ ነው የሚሉት ሊሰራ የሚችለው እነሱን ከጠቀመ  ብቻ  እንደሆነ ካወቅን ውሎ  አደረ። ካልሆነ ይሻራል። 
ሚካኤል ፖሊስ ቀጥሮ የቦርድ አባላት እንዳይሳሳቱ ሃጥያት እንዳይሰሩ ለማድረጉ ደግሞ ባለፈው የተፈጠረውን  የቦረዱን አባል የሴትኛ አዳሪ አፈላማ እንደ ማስረጃ ያወሱናል ይህ ደግሞ  ቤት ሊሰብሩ የሚሄዱ ወይም ኪስ ለማውለቅ የሚሄዱ ሌቦች ለጊዮርጊስ ይሳላሉ የሚለውን አባባል ያስታውሰናል። 

ትላንት አባል ካልሆናችሁ ብለው ይናገሩ የነበሩትን ግለሰቦች ክስ ከመሰረቱት ውስጥ   አንዱ ሲመልሱ "አንድ ሰው አባል የሚሆነው እኮ መብት ካለው ብቻ ነው። እኛ ከቤተክርስቲያን በፖሊስ የተባረርነው አባል ሆነን እኮ ነው።
አትናገሩም የተባልነው አባል ሆነን ነው።
ስብሰባ  አይጠራላችሁም የተባልነው 126  አባላትን አስፈርመን  እኮ  ነው"
ብለው ሲናገሩ አድምጠን ነበር። አሁንም ያ ድርጊት ሲደገም እያስተዋልን ነው።

ሽምግሌ  የማይቀበሉ
የአባላትን ፊርማ አሽቀንጥረው የሚጥሉ
ለቤተክርስቲያኑ የምናስበው እኛ እንጂ ብዙሃን አይደሉም የሚሉ
እነሱ ከስደት ሲኖዶስ ጋር እየተነጋገሩ ከሳሾች ቤተክርስቲያናችሁን ነጥቀው ለኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሊሰጡባችሁ ነው እያሉ የሚቀጥፉ
የነሱን የፖለቲካ ሽኩቻ ይዘው መምጣታቸውን ደብቀው የሌለ ኢሕአደግ እየመጣባችሁ ነው ብለው የሚያስፈራሩ
በፖለቲካ ዓለም ማንም ፓርቲ መመሪያና መርህ እንዳለው ሳይናገሩ ከሳሾች 52 ነጥብ አስፈጻሚዎች ናቸው ብለው ሲወነጅሉ ቅር የማይላቸው።
ኢትዮጵያ ያለው መንግሥት ገንዘብ አጥቶ የቤተክርስትያኑን (የከፈሉበት ይመስል) $400,000 ለመውሰድ እየሸረበ  ነው ብለው ሊያሳምኑ የተነሱ
ትላንት ያወድሷቸው የነበሩትን ግለሰቦች አሁንስ አበዛችሁት ሲሏቸው 360 ዲግሪ ተሽከርክረው ዘራቸውን እየቆጠሩ ሲሳደቡ ቅር የማይላቸው የቦርድ አባላትና ደጋፊዎቻቸው
ማ ከማ ጋር አንሶላ  ተጋፈፈ  ብለው ሲያወሩን የነበሩ መሪዎችና ደጋፊዎቻቸው
የነፍስ ግድያ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦችን እናውቃለን በማለት ስም እየጠቀሱ የመያውቁትን ፈጥረው ያልተባለ  ቀጥለው ያሰራጩ
ያልደገፏቸውን ግለሰቦች ትዳራቸው እንዲፈርስ ሚስቶቻቸውንና ባሎቻቸውን እርጃ ውሰዱ (ተለያዩ)  ያሉ ግለሰቦች
ዛሬ  ልብ ገዝተው ፈሪሃ  እግዚአብሄር አድሮባቸው ካለ  ፍርድ ቤት ትእዛዝ ምርጫ አስቁመው የሕዝቡን ቃል ያከብራሉ ማለት ለኛ አይዋጥልንም።

ሆኖም ፊርማ ሲያስፈርሙ የከረሙት ወንድሞችና እህቶች አሁንም ቦርዱን በመጠየቅ በማነጋገር መስመር ማስያዝ ይቻላል ማለታቸውን ስንሰማ በተአምር እናምናለንና ይሳካላችሁ ብለናል።

ውድ አንባብያን በሚመጣው ሳምንት 1/23/11 እሁድ በሚደረገው ስብሰባ ላይ ሙሉ ገለጻ እንደሚደረግ የገለጹልን የመብት አስከባሪ ቡድኖች ሁላችሁም እንድትገኙ በድጋሜ ጥሪ ያደርጋሉ።

ሚካኤል ፈቃዱ ከሆነ ምናልባት የምስራች ይኖረን ይሆናል።

የሳምንት ይበለን

Wednesday, January 12, 2011

የስብሰባ ጥሪ እንደገና

ጠቅላላ የምእመናን ስብሰባ ጥሪ”



ተፈጥሮ በነበረው ሐዘን ምክንያት የተሰረዘው የምእመናን ስብሰባ ጥሪ እንደገና እየተጠራ ነው።

ሁላችሁም ስብሰባውን ለመካፈል ተዘጋጁ!!!

 
ቀኑ፡- ጥር ፲፭ ቀን ፳፻፫ እሑድ


January 23, 2011, Sunday


ሰዓት፡-1፡00 P.M    

ምሳ አለ።


ቦታው፡- Dream Club

7035 Greenville Ave #E

Dallas, TX 75231-5109

በበለጠ ለመረዳት

በ(214) 368-4981

ወይንም

(469) 879-8650 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።


የተባለውን ለመስማት ብቻ  ሳይሆን የራሳችሁን ሃሳብ

ለማካፈልም ወደ ስብሰባው መምጣት የግድ ነው።

ላልሰሙ ሁሉ ተናገሩ።

እንደገና  ተላልፎ  የነበረው ስብሰባ
 በድጋሜ ተጠራ።

የመልአኩ እርዳታ ይታከልበት። በችግር ምክንያት መምጣት የማትችሉ ብትኖሩ በጸሎታችሁ አስቡን።

ከየቅዱስ ሚካኤል የሰላምና የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ የቀረበ።





Wednesday, January 5, 2011

ዝም ያለ ሰው እያዳመጠ እንጂ መናገር አቅቶት አይደለም። ቁጥር ፶፭

ሰሞኑን ከአንባብያን ለደረሱንን የድጋፍ መግለጫዎች ሁሉ እያመሰገንን ለተሰደቡት ብርታትን፣ ለተወነጀሉት ጽናትን፣ ይስጣቸው እንላለን። ብዙዎቻችሁ በመረዋ ላይ መግለጫ ለመለጠፍ ጠይቃችሁን ነበር። ነገር ግን የመረዋ አነሳስም ሆነ ጉዞ የፖለቲካ ስንክሳር ለማራመድ ባለመሆኑና የአንባቢዎቻችንን ፍላጎትም በመገንዘብ ከአጀማመሩ ያ እንዳይሆን አቋም የወሰድንበት ጉዳይ ስለሆነ ጥያቄአችሁን ባለመቀበላችን ይቅርታ  እንጠይቃለን። ያም ቢሆን ለተሰደቡ ደጋፊዎቻችን ያለንን አድናቆት እየገለጽን የተሰደባችሁትና በሃሰት የተወነጀላችሁት እውነት በመናገራችሁ፤ ለመብት በመቆ ማችሁ በመሆኑ ልትኮሩ እንጂ ልታፍሩ አይገባችሁም እንላለን። እውነት የሆነውን ሁሉ ብንጽፍ ደግሞ በሃሰት  የተሰለፉትን ከስራ ማፈናቀል ይሆናል። ለመብት የቆሙ ደግሞ ጠንካሮች እንደሆኑ ማስረጃ የሚያስፈልግ አይሆንም። በየቀኑ የምታሳዩን እውነታ ነውና። እናንተን እያየን በየቀኑ እየተማርን ነው። መረዋ እውነትን ይዘው ከቆሙት ጎን በመቆሙ አሁንም ደስተኛ ነው። እውነት ለማሸነፉ ደግሞ ጥርጥር የለንም።

ዛሬ ከመረዋ  ከሰነበቱ እትሞች አለፍ አለፍ እያልን ልናስነብባችሁ እንወዳለን።ያለፈውን በማየት መጭውን ዳግም እንድናቃኝ ይረዳናልና።


ከመረዋ  ቁጥር ፩
11/26/09

"አሁን ለምን ሽማግሌዎች ሊያስታርቁ ተነሱ" ብሎ መተቸትና መሰናክል ለመፍጠር መነሳት ግን ሌላ ስህተት ነው ብለን ደግሞ እናምናለን። በፍርድ ቤት ትእዛዝ ችግራችን ይፈታል ብሎ የሚያምን ካለ የዋህ ነው ብሎ መናገር ማስፈራት የለበትም። ፍርድ ቤት በሚሰጠው ብያኔ ፍቅር አይመጣም አንድነት አይፈጠርም። ይህ ሊሆን የሚችለው የተለያየ ሃሳብ ይዞ የሚከራከረው ቡድን ተቀምጦ መነጋገር ሲችል ብቻ ነው። ክስ የመሰረቱትን ለምን ክስ መሰረቱ ብሎ መኮነን ደግሞ ሲደረግ የነበረውን መካድ ይህንን ባያደርጉ ኖሮ ዛሬ እንደዚህ ለመናገር የማንችልበት ሁኔታ ላይ እንሆን እንደነበር አለመቀበል ይሆናል። የቤተክርስቲያን ገንዘብ ስላለ ከሳሾቹን ገንዘባቸውን አስጨርሰን እንዲሸነፉ እናደርጋለን የሚሉት የቤተክርስቲያኑ ተመራጮች ማወቅ ያለባቸው ነገር ቢኖር የተመኩበት ገንዘብ ከምእመናን የተዋጣ መሆኑን ነው። ምእመኑ ካልደገፈ የገንዘቡ ቌት እንደሚሟጠጥ ከሳሾችንም ከአሁኑ በበለጠ እየደጎሙ እየደገፉ እንዲቀጥሉ ሊያበረታቱ እንደሚችሉ ማሰብም የተገባ ነው። ከሳሶችም ሆኑ የቤተክርስቲያኑ ተመራጮች ማወቅ ያለባቸው ነገር ቢኖር ያለ ምእመን ድጋፍ የትም ሊሄዱ እንደማይሄችሉ ነው። በተናጠል ቤተክርስቲያን አይገነባምና። ተሰዳደብን፡ ተካሰስን፡ ተወነጃጅለን አሁን ደግሞ ወደ አንድነት ለመምጣት ምን አስተዋጽኦ እናድርግ ብሎ መነሳት ክርስቲያናዊ ነውና ሁላችንም በተናጠል እራሳችንን ጠይቀን ለሰላም እንነሳ። እከሌን ብናገረው እንጣላለን ከመሃበር ያባርሩኛል ያልሆንኩትን ስም ይሰጡኛል፡ ዝምድናችን ይፈርሳል ጔደኝነታችን ይቀራል በቡድን ያጠቁኛል ብሎ በመፍራት ለእውነትና ለመብት አለመነሳት ደግሞ በሕሊና ማስጠየቅ ይኖርበታል እንላለን። ስለሆነም ለሁላችሁም ዛሬ ጥያቄዎች ማቅረብ እንወዳለን። በግል ምን እያደረግን ነው? ሰለኛ ሌሎች እስከመቼ ይወስናሉ?መብትና እምነት፡ ሕግና አምልኮን መለየት የምንችለው መቼ ነው?

ወንድሞችና እህቶች ይህ ከዚህ በላይ ያነበባችሁት መረዋ የመጀመሪያ እትምቱን ሲያወጣ የዘገበው ነው። እኛ ዛሬ ስናነበው የዛሬ ጽሑፍ መሰለን እናንተስ?

ከመረዋ  ቁጥር ፵፬ ደግሞ  እስቲ እናንብብ
10/06/10

 
ይህ ክስ አባላትን ማባረር ከጀመሩ በኋላ የተመሰረት መብትን ለማስከበር የተመሰረት ክስ መሆኑም ለሁላችንም ግልጽ ነው።
ስለሆነም በነገው እለት ምንም ተፈጠረ ምን
መተዳደሪያ ደንቡ ወደነበረበት ካልተመለሰ
የተባረሩ አባላት ካልተመለሱ
የአባላት ክፍያ ወደነበረበት ካልተመለሰ
አንዱ ልጅ ሌላው እንጀራ ልጅ መሆኑ ካልቀረ

የአባላት መብት ካልተጠበቀ
ፖለቲከኞች ከቤተክርስቲያን ውስጥ ፖለቲካቸውን ካላቆሙ
የምእመናንን ጥቅም አስከባሪ ቦርድ እስካልተቋቋመ
ብሎም
ባለፈው እንዳደረጉት ቦርዱ በመሰብሰቢያ አዳራሻቸው እነ አቶ ሃይሉ እጅጉን ጠርተው እየተሳደቡት ክስ ከመሰረቱት ውስጥ ነህና ካላረፍክ እንከስሃለን የክስ አጋሮችህንም አብረን ለፍርድ እናቆማለን እንዳሉት በተናጠል ማስፈራራት እስካላቆሙ ድረስ
በቦርዱ ብሎግ መሳደባቸውን እስካልገቱ ድረስ
መታገላችንን አናቆምም


አንዳዴ  ትላንት የተጻፉ ጽሑፎች ዛሬም እንዳዲስ የዛሬውን የሚተርኩ ይመስላሉ።

ይህንን ዳግም ልናስነብባችሁ የተነሳነው መረዋ ትላንትና የዘገበው ዛሬም እውነት መሆኑን ለአንባቢዎቻችን ለማስይረዳል ይጠቅማል ብለን በማሰብ ነው። ከሳሾች በስድብ አልደነበሩም። በማስፈራራት አልተበተኑም። በውሸት ወሬ አልበረገጉም። የሚንበረከኩት ለፍቅር፤ ለእውነት ለመሆኑ ደግሞ ጥርጥር የለንም። ይህንንም በተደጋጋሚ ሊያወያዩ ለተነሱ አዛውንቶች ሁሉ ያረጋገጡት ለመሆኑ መስካሪዎቹ አዛውንቶቹ ይሆናሉ እንላለን። በመወያየት የሚያምኑት የከሳሽ ወገኖች የሚያሸንፉትም ሆነ የሚሸነፉት በውይይት ብቻ እንደሆነ ያምናሉ። ለካሳ አልተነሱም፡ ለመብት መከበር እንጂ። አማንያንን ለመበታተን አልተነሱም የተበተነውን ለመሰብሰብ እንጂ። ለመከፋፈል አልተነሱም አንድነትን ለመፍጠር እንጂ። ይህ ደግሞ ሊመጣ የሚችለው በመነጋገር ብቻ እንደሆነ  ጥርጣሬ  የላቸውም።   የመነጋገር በሩ ከተዘጋ ግን አማራጩ አንድ ብቻ ይሆናል። መብትን በፍርድ ቤት ማስከበር ብቻ። ይህ ሳይሆን ክሱን ተው ብሎ መጠየቅ ግን "ታንክ ከያዘ ጠላት ፊት ቡጢ ይዛችሁ ቅረቡ" እንደ ማለት  ይመስላል።
ከሳሽ የምንላቸው ግለሰቦች ገንዘባቸውንና ጊዜአቸውን የማባከን ሱስ የለባቸውም። ለመብታቸው ትግል ባይጀምሩ ኖሮ ግን እንደማይሰደቡም ያውቃሉ። እንደ ቦርድ አባላት በ ሺ የሚቆጠር እንደፈለጉት የሚያጠፉት የባንክ ደብተርም የላቸውም። ከደጋፊዎች የሚሰበሰብ የድጋፍ መዋጮ እንጂ። ታዲያ የሚያገኙት ምንድነው ለሚሉ ግለሰቦች መልሱ መብታቸውን ማስከበ ይሆናል። ትላንት ፍርድ ቤት ባይሄዱ ኖሮ   81 የቤተክርስቲያን አባላት ከቤተክርስቲያን በፖሊስ ተባረው ነበር። ፍርድ ቤት ባይሄዱ ኖሮ ቤተክርስቲያን ለአምልኮ እንኳን እንዳይደርሱ ተከልክለው ነበር። ይህንን እንዳያደርጉ በፍርድ ቤት ሲታዘዙ አይደለም እንዴ የቦርድ አባላት ይግባኝ ብለው ዛሬም የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤትን ውሳኔ በጉጉት የሚጠብቁት። ለምን እንደባበቃለን። ከሳሾች አባላት አይደሉም አናውቃቸውም ያሉት የቦርድ አባላት አይደሉምን?ለምን እንደባበቃለን። ከሳሾች የጀርመን ናዚ ፋሽስት የወጣት አባላት አይነት ናቸው ብለው ለፍርድ ቤት ቃላቸውን የሰጡት አሁንም የቦርዱ አባላት አይደሉምን?
ለምን እንደብቃለን? ከሳሾች ልጆች እንደሌላቸው ሁሉ፣ ሕጻናቶችን ከጫማ ጋር ከፎቅ ላይ ወደ መሬት ሊወረውሩ ነበር ተብለው በፍርድቤት አልተወነጀሉምን? ይኸ ልክ አይደለም ያሉ ሁሉ ከሳሾችን ለመርዳት ቃል እንዲገቡ አደረጋቸው እንጂ እነሱ እንዳሰቡት ደጋፊ አላሳጣቸውም። የቦርድ ደጋፊ ነን ባይ ጦማርም "they are  inocent till they are prooven  gilty"  ሲሉ አላዳመጥንም። ብቻ  ሆድ ይፍጀው። አገሩ ደግሞ  የዲሞክራሲና  የመብት አገር የሕግ የበላይነት ያለበት ምድር መሆኑ እረዳን።

ይህንን በዚህ እናጣፋና ወደ ሌላ ጉዳይ እንግባ

ከዚህ በፊት በደረሰው በወጣቱ ሐዘን ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተላልፎ የነበረው የተባበሩት የሰላምና ፍትሕ አስተባባሪ ኮሚቴ  አጠቃላይ ስብሰባ እሁድ
January  23, 2011 ከቀኑ 1:00 PM
በ DREAMZ CLUB 
እንደሚደረግ የደረሰን ማሳሰቢያ ይገልጻል። በወቅቱ ከስብሰባው በፊት ምሳ  እንደሚኖርም ለመረዳት ችለናል።

ሳንረሳው መጥቀስ የምንወደው ሌላ ጉዳይ አለ። ሰሞኑን በሌላው ጦማር እንደ ተለመደው በአቶ ተኮላ መኮንን ላይ የተሰነዘረውን የሃሰት ውንጀላ አስመልክቶ የተጻፉ መልሶች

 በ WWW.ASSIMBA.COM

እየተለጠፉ እንደሆነ መገንዘባችንን ለአንባቢዎቻችን እንገልጻለን።



የከርሞ ሰው ይበለን።