Monday, January 24, 2011

በትላንትናው ቀን የተጠራው ስብሰባ በሙሉ መግባባት ተፈጸመ።

ባለፈው እንደ ነገርናችሁ በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰላም መፍተሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በትላንትናው እለት ጠርቶት የነበረው ስብሰባ በመግባባትና በሙሉ ስምምነት መገባደዱን የደረሰን ዜና አስታውቋል። በወቅቱ በተደረገው ስብሰባ  የተገኙት እንግዶች ከምሳ ግብዣው በኋላ ሰፊ ውይይት እንዳደረጉ ሲነገር፣ በወቅቱ የአራቱም የኮሚቴው ተወካዮች በየተራ  ለተሰብሳቢው ስለተደረገው ያለፈ የኮሚቴ የስራ ክንውን መግለጫ መሰጠታቸውንም ለመረዳት ችለናል። በዜናችን መሰረት የመንፈሳዊ ኮሚቴ አባላት ከቤተክርስቲያናችን እየተገፉ የሚገኙትን አባላት መንፈሳዊ ጽናታቸን ለማጠናከር በዓርብ ምሽት የሚደረጉትን ትምህርቶች በየሰዎስት ወሩ የተዘጋጁትን የመንፈሳዊ ጉባኤዎች በሚያስደንቅ መልኩ ማካሄድ እንደቻሉ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ይህንንም ማድረግ የተቻለው ዓርብ ማታ በሚደረገው መንፈሳዊ ትምህርት ተካፋዮች ጉልበትና ከኪስ በተዋጣ ወጭ እንደ ሆነም የኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ተናግረዋል። በወቅቱ ኮሚቴውን በማሰባሰብና በማስተማር በመምራት ያገለገሉት ከቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በሌሊት በፖሊስ ተከበው የመሰናበቻ ወረቀቱን እንዲፈርሙ የተገደዱትና፡ ከቤተክርስቲያኑ ቦርድ ለኢሚግሬሽን በተጻፈ  ደብዳቤ  የኢምግሬሽናቸው ሁኔታ እንዲታገድና ከአገር ከነቤተሰባቸው እንዲባረሩ የተጠየቀባቸው መላከ ሳህል አወቀ ሲደልል እንደ ነበሩ ለተሰብሳቢዎቹ ተናግረዋል። በአሁኑ ሰዓት መላከ ሳህል አወቀ አትላንታ የሚገኝ ደብር ቀጥሯቸው ወደ አትላንታ መሄዳቸውም ለተሰብሳቢው ተገልጿል። ስለሆነም ቀደም ብለው ወደ አዲሱ ሥራቸው የተዛወሩት መላከ ሳህል አወቀ የዳላስን ምእመናንን ለመጨረሻ ጊዜ ለመሰናበት በፊታችን ዓርብ 1/28/2011ዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ባሻገር በሚገኘው የኬንያውያን ቤተክርስቲያን አዳራሽ ውስጥ እንደሚገኙ ሲነገር፡ ማንኛውም ምእመን ቤተሰባቸውንና እሳቸውን ለመሰናበት በዚሁ እለት እንዲገኝ ኮሚቴው ለሁሉም የዳላስ ምእመን ጥሪውን አቅርቧል። በዚህ አጋጣሚ መረዋ ለኝህ ቆራጥ ካህን ያለውን አድናቆትና ያላቸውን ቆራጥነት እያደነቀ፤ መጭው የሥራ ቦታቸው የተቃና እንዲሆን ምኞቱን ይገልጻል። መላከ ሳህል አወቀ እንደ አባት የሚርቁብን ቢሆንም ምሳሌነታቸው ግን ከልባችን ለዘላለም ይኖራል። የመንፈስ አባቶ ችን ስናነሳም እንደ ምሳሌ የምንጠቅሳቸው ይሆናሉ። ለቤተሰቦቻቸው ያለንንም አድናቆት ስንገልጽ በደስታ ነው። በተለይ ለውድ ባለቤታቸው መረዋ ያለውን አክብሮትና የመንፈሰ ጠንካራነት አርአያ መሆናቸውን መመልከቱን ሲጠቅስ በኩራት ነው።

የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ተዋካይ ደግሞ በተለያየ መንገድ ለአባላት የተላኩ መልእክቶች እንዲዳረሱ ማድረጉን በመናገር የኮሚቴው ልሳን የሆነው WWW.MELEKET4U.BLOGSPOT.COM ከመቼውም በበለጠ ከዚህ በፊት የተደረጉትንም ሆነ ወደፊት የሚደረጉትን ለአባላት ለማስነበብ በገጹ ላይ እንደሚለጥፍ ቃል ከመግባቱ ባሻገር ከብሎግ አልፎ WEB PAGE ወደፊት ለማውጣት እቅድ ላይ መሆኑን ተናግሯል።

የአባላት ኮሚቴ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት የደጋፊዎቻችን ቁጥር ከ200በላይ እንደሆነ  በመጠቆም አሁንም ከሌላው ወገን የሚሰነዘረውን የውሸት ወሬና ስድብ በተቋቋምን ቁጥር ካስተዋልኩት ደጋፊዎቻችን እየበዙ መሄዱን አውቃለሁ በማለት ጠቁመዋል። ለዚህም ዋናው መሳሪያችን ሲሳደቡ አለመሳደባችን፣ አለመዋሸታችን፣ ስንጀምር ያነሳነው የመብት ጥያቄ አሁንም በእንጥልጥል መሆኑና አለመዋዠቃችን  እንደሆነ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል።

የሕግ ኮሚቴ ተወካይ በበኩላቸው ቤተክርስቲያን እንዴት ይከሰሳል የሚሉት ግለሰቦች ለምን የአባላት መብት ይደፈራል? ሲሉ ያለመሰማታቸውን ተናግረው፡ ለመብት እንቆማለን ያለ ማንም ግለሰብ መብቱ ሲጣስ ያለው አማራጭ በጉልበት መጠቀም ሳይሆን በሕግ መከላከል ብቻ ነው፥ ብለው የሚገርመው ቤተክርስቲያንችን ተከሰሰ  ያሉት የቦርድ  አባላት ባዲስ መልክ እንደ መከላከያ ያመጡት ነጥብ ቢኖር በቦርድ አባልነታችን በግል መከሰስ የለብንም ቢፈልጉ ከሳሾች ቤተክርስቲያኑን ይክሰሱ ብለው ፍርድ ቤቱን መጠየቃቸው እንዳስገረማቸው ተናግረዋል። ሆኖም ከትላንትናው በተሻለ ሁኔታ ጉዳዩ እየተፋጠነ መሆኑን አብራርተው ስለፍርድ ቤቱ ሁኔታ አጭር ገለጻ አድርገዋል፡፡

በገለጻቸው መሰረት ከዚህ በፊት ዳኛው  ምእመንን ከቤተክርስቲያን አትከልከሉ። ፖሊስ ወደ መቅደስ አታስገቡ። ዶሴዎችና ማናቸውንም መረጃዎች አታጥፉ ብለው ያዘዙትን  ትእዛዝ አንስማማም በማለትምእመንን የማባረር መብት አለን፣ ፖሊስ በመቅደስ ውስጥ  ማስገባት አለብን፣ ዶሴዎችንና ማናቸውንም መረጃዎች እንድናጠፋ ይፈቀድልን፣ ብለው ይግባኝ ባሉት መሰረት በ 2/7/2011 3:00PM ላይ በ ይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት 3 ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የከሳሽና የተከሳሽ ጠበቆች 30 ፤ 30 ደቂቃ ተሰጥቷቸው ክርክር ስለሚያደርጉ ማንኛውም ሰው፥
600 COMMERCE DALLAS COUNTY COURT BUILDING 2nd FLOOR በመገኘት ማዳመጥ  እንደሚችል ተናግረዋል።

በተጨማሪ በ 2/10/2011 192court በመገኘት ባለፈው እረዳት ዳኛ በቦርዱ ላይ የፈረዱባቸውን የከሳሾችን ጥያቄዎች እንዲመልሱ የታዘዙትን ቦርዱ አሻፈረኝ ብሎ  ይግባኝ ባለው መሰረት ዳኛ ስሚዝ ፊት ቀርበው የሁለቱም ጠበቆች እንደሚከራከሩ ስንነግራችሁ አሁንም የምትችሉ ሁሉ ከላይ ባለው አድራሻ በ 9:00 AM በመገኘት እንድታዳምጡ ብለው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። አያይዘውም ዳኛው በዚህ ጉዳይ ላይ የሚሰጡት ብይን ይግባኝ የሌለውና የመጨረሻ  መሆኑንም ለተሰብሳቢዎቹ ተናግረዋል።

በመደምደሚያው የስብሰባው ሰብሳቢ፣ ሁሉም ላደረጉት እርዳታ ከልብ መነካታቸውን ተናግረው ለመብት አለመቆም በራሱ ድክመት መሆኑን  ተናግረዋል። በተለያየ  መንገድ እርዳታ የሚያደርጉትን ግለሰቦች አመስግነው አሁንም እርዳታው እንዲቀጥል አሳስበዋል።

መረዋ ሁላችሁንም በተባሉት የፍርድ ቤት ቀጠሮዎች እንድትገኙ  ጥሪውን እያስተላለፈ ለዛሬው በዚሁ እንሰናበታችኋለን።

የሳምንት ሰው ይበለን።

Friday, January 14, 2011

የተናገርነው እየተፈጸመ በመሆኑ ትንቢተኞች ነን አላልንም።

ሰላምና  ፍቅር ለሁላችሁ ይሁን አንባብያን እንዴት ከረማችሁ።

አንድ ነገር ዛሬ ደጋግመን ደጋግመን መናገር የምንወደው ነገር አለ። መረዋ እንደ ጦማር መውጣት ከጀመረበት ሰዓት ጊዜ  ጀምሮ የዋሸነውና አንባቢዎቻችንን ያደናገርንበት ጊዜ የለም። ከጅምሩ ስንለው የነበረው ነገር በሙሉ እየተፈጸመ ስናይ ደግሞ ትንቢተኞች ነን ብለን አልተመጻደቅንም። እትምት ላይ የምናመጣውን ማናቸውንም ነገር ግራና ቀኝ ሳናገናዝብ ጽፈን አናውቅም። አጀማመራችን ለጉራ ሳይሆን ባለፈው እንዳልነው መረዋ ሞተ የምንለው ውሸት ይዞ የተነሳ እለት ነው ብለን ስለምናምን መጠንቀቃችንን ለናንተ ለማረጋገጥ ነው። ዛሬ የተለየ ዜና ይዘንላችሁ አልቀረብንም። ስትሰሙት የከረማችሁትን እንጂ። ባለፈው ሳምንት ከእትምት እንድንቆጠብ በተጠየቅነው መሰረት ቃላችንን ፈጽመናል። ያን ስናደርግ ደግሞ ለውጥ ይመጣል ብለን አስበን እንዳልነበረ ልታውቁልን ይገባል። ያ የገባንው ቃለ  ቀጠሮ  ሲያከትም እነሆ እትምታችንን ጀምረናል።

ሰሞኑን ምርጫ ለማካሄድ የቦርድ ተመራጮች ደፋ ቀና እያሉ ነው። የፖለቲካ ድርጅቶችም ይወክሉናል የሚሏቸውን ለምርጫ አሰልፈዋል። እነማን እንደሆኑ ደግሞ ያነበባችሁትና የሰማችሁት ጉዳይ ነው።አዲሶች ተመራጮች ሆነው የቀረቡት ግለሰቦች ትልቅ ሹመት የሚያገኙ መስሏቸው ተነስተው ከሆነ ትልቅ ስህተት እየተሳሳቱ ነው። እየነደደ  ባለ ቤት ነዳጅ ይዞ  መግባት እሳቱን ማፋጠን እንጂ የሚያጠፋው አይሆንም። መቃጠሉ ይሻላል የሚሉ ከሆነ ሹመት ያዳብር እንላቸዋለን።

ምርጫውን ለማስቆም ከ 60 በላይ የሚሆኑ የቤተክርስቲያኑ አባላት በፊርማ ቦርዱን እንደጠየቁም ሰምተናል። ምላሹ ምን ይሆን? ብለው የጠበቁ ካሉ አናውቅም እንጂ እኛ እንቢ እንደሚሏቸው እርግጠኞች ነበርን። እንዳልነውም የቦርዱ አባላት የተሰጣቸውን ፊርማ ወርውረው ምክንያት እየፈጠሩ ምርጫውን ማስቆም የሚችል ምንም ሃይል አይኖርም ማለታቸውን ሰምተናል። የፈራሚዎቹ አባላት ሌላ የምንጠይቀው አለን እኛ በእግዚአብሄር ቤት ተስፋ አንቆርጥም ማለታቸውንም ከተጨባጭ ምንጮች የደረሰን ዜና አብስሮናል። ሚካኤል ይርዳቸው እንላለን። እኛ ግን መብትን ማስከበር የሚቻለው በሕግ ብቻ  እንደሆነ  ከተቀበልን ቆይተናልና ከሕግ ወጪ ለውጥ እንደማይመጣ ከተገነዘብን ውሎ  አደረ። ለዚህም ነው መረዋ ክስ የመሰረቱት ግለሰቦች የመክሰስ ሱስ ይዞአቸው ሳይሆን መፈናፈኛና አማራጭ አጥተው ነው በማለት ከሳሶችን ደግፎ  የተነሳው።

ከሳሾች አባል አይደሉም ያሉ የቦርድ ተመራጮች አባል ያልሆኑትን ለቦርድ እጩ አድርገው እያቀረቡ ነው።
የአባላትን ቁጥር ለማብዛት ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አባላትን እየተዋሱ እንደሆነም እየተመለከትን ነው።
የጊዮርጊስ አስመራጭ ኮሚቴ አባል የሚካኤል እጩ የሆኑት ባለቤታቸው ጊዮርጊስ ስላልተመረጡ ተናደው ነው ሲባል አልሳቅንም ቀልዳችሁን ነው አልን እንጂ።  
በኮሚቴ አባልነት ያላገለገሉ ተመራጭ ሆነው ሲቀርቡ ምነው?  አላልንም የምናውቀውን አጠናከረልን እንጂ። የራሳችን መተዳደሪያ ሕግ ነው የሚሉት ሊሰራ የሚችለው እነሱን ከጠቀመ  ብቻ  እንደሆነ ካወቅን ውሎ  አደረ። ካልሆነ ይሻራል። 
ሚካኤል ፖሊስ ቀጥሮ የቦርድ አባላት እንዳይሳሳቱ ሃጥያት እንዳይሰሩ ለማድረጉ ደግሞ ባለፈው የተፈጠረውን  የቦረዱን አባል የሴትኛ አዳሪ አፈላማ እንደ ማስረጃ ያወሱናል ይህ ደግሞ  ቤት ሊሰብሩ የሚሄዱ ወይም ኪስ ለማውለቅ የሚሄዱ ሌቦች ለጊዮርጊስ ይሳላሉ የሚለውን አባባል ያስታውሰናል። 

ትላንት አባል ካልሆናችሁ ብለው ይናገሩ የነበሩትን ግለሰቦች ክስ ከመሰረቱት ውስጥ   አንዱ ሲመልሱ "አንድ ሰው አባል የሚሆነው እኮ መብት ካለው ብቻ ነው። እኛ ከቤተክርስቲያን በፖሊስ የተባረርነው አባል ሆነን እኮ ነው።
አትናገሩም የተባልነው አባል ሆነን ነው።
ስብሰባ  አይጠራላችሁም የተባልነው 126  አባላትን አስፈርመን  እኮ  ነው"
ብለው ሲናገሩ አድምጠን ነበር። አሁንም ያ ድርጊት ሲደገም እያስተዋልን ነው።

ሽምግሌ  የማይቀበሉ
የአባላትን ፊርማ አሽቀንጥረው የሚጥሉ
ለቤተክርስቲያኑ የምናስበው እኛ እንጂ ብዙሃን አይደሉም የሚሉ
እነሱ ከስደት ሲኖዶስ ጋር እየተነጋገሩ ከሳሾች ቤተክርስቲያናችሁን ነጥቀው ለኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሊሰጡባችሁ ነው እያሉ የሚቀጥፉ
የነሱን የፖለቲካ ሽኩቻ ይዘው መምጣታቸውን ደብቀው የሌለ ኢሕአደግ እየመጣባችሁ ነው ብለው የሚያስፈራሩ
በፖለቲካ ዓለም ማንም ፓርቲ መመሪያና መርህ እንዳለው ሳይናገሩ ከሳሾች 52 ነጥብ አስፈጻሚዎች ናቸው ብለው ሲወነጅሉ ቅር የማይላቸው።
ኢትዮጵያ ያለው መንግሥት ገንዘብ አጥቶ የቤተክርስትያኑን (የከፈሉበት ይመስል) $400,000 ለመውሰድ እየሸረበ  ነው ብለው ሊያሳምኑ የተነሱ
ትላንት ያወድሷቸው የነበሩትን ግለሰቦች አሁንስ አበዛችሁት ሲሏቸው 360 ዲግሪ ተሽከርክረው ዘራቸውን እየቆጠሩ ሲሳደቡ ቅር የማይላቸው የቦርድ አባላትና ደጋፊዎቻቸው
ማ ከማ ጋር አንሶላ  ተጋፈፈ  ብለው ሲያወሩን የነበሩ መሪዎችና ደጋፊዎቻቸው
የነፍስ ግድያ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦችን እናውቃለን በማለት ስም እየጠቀሱ የመያውቁትን ፈጥረው ያልተባለ  ቀጥለው ያሰራጩ
ያልደገፏቸውን ግለሰቦች ትዳራቸው እንዲፈርስ ሚስቶቻቸውንና ባሎቻቸውን እርጃ ውሰዱ (ተለያዩ)  ያሉ ግለሰቦች
ዛሬ  ልብ ገዝተው ፈሪሃ  እግዚአብሄር አድሮባቸው ካለ  ፍርድ ቤት ትእዛዝ ምርጫ አስቁመው የሕዝቡን ቃል ያከብራሉ ማለት ለኛ አይዋጥልንም።

ሆኖም ፊርማ ሲያስፈርሙ የከረሙት ወንድሞችና እህቶች አሁንም ቦርዱን በመጠየቅ በማነጋገር መስመር ማስያዝ ይቻላል ማለታቸውን ስንሰማ በተአምር እናምናለንና ይሳካላችሁ ብለናል።

ውድ አንባብያን በሚመጣው ሳምንት 1/23/11 እሁድ በሚደረገው ስብሰባ ላይ ሙሉ ገለጻ እንደሚደረግ የገለጹልን የመብት አስከባሪ ቡድኖች ሁላችሁም እንድትገኙ በድጋሜ ጥሪ ያደርጋሉ።

ሚካኤል ፈቃዱ ከሆነ ምናልባት የምስራች ይኖረን ይሆናል።

የሳምንት ይበለን

Wednesday, January 12, 2011

የስብሰባ ጥሪ እንደገና

ጠቅላላ የምእመናን ስብሰባ ጥሪ”



ተፈጥሮ በነበረው ሐዘን ምክንያት የተሰረዘው የምእመናን ስብሰባ ጥሪ እንደገና እየተጠራ ነው።

ሁላችሁም ስብሰባውን ለመካፈል ተዘጋጁ!!!

 
ቀኑ፡- ጥር ፲፭ ቀን ፳፻፫ እሑድ


January 23, 2011, Sunday


ሰዓት፡-1፡00 P.M    

ምሳ አለ።


ቦታው፡- Dream Club

7035 Greenville Ave #E

Dallas, TX 75231-5109

በበለጠ ለመረዳት

በ(214) 368-4981

ወይንም

(469) 879-8650 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።


የተባለውን ለመስማት ብቻ  ሳይሆን የራሳችሁን ሃሳብ

ለማካፈልም ወደ ስብሰባው መምጣት የግድ ነው።

ላልሰሙ ሁሉ ተናገሩ።

እንደገና  ተላልፎ  የነበረው ስብሰባ
 በድጋሜ ተጠራ።

የመልአኩ እርዳታ ይታከልበት። በችግር ምክንያት መምጣት የማትችሉ ብትኖሩ በጸሎታችሁ አስቡን።

ከየቅዱስ ሚካኤል የሰላምና የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ የቀረበ።





Wednesday, January 5, 2011

ዝም ያለ ሰው እያዳመጠ እንጂ መናገር አቅቶት አይደለም። ቁጥር ፶፭

ሰሞኑን ከአንባብያን ለደረሱንን የድጋፍ መግለጫዎች ሁሉ እያመሰገንን ለተሰደቡት ብርታትን፣ ለተወነጀሉት ጽናትን፣ ይስጣቸው እንላለን። ብዙዎቻችሁ በመረዋ ላይ መግለጫ ለመለጠፍ ጠይቃችሁን ነበር። ነገር ግን የመረዋ አነሳስም ሆነ ጉዞ የፖለቲካ ስንክሳር ለማራመድ ባለመሆኑና የአንባቢዎቻችንን ፍላጎትም በመገንዘብ ከአጀማመሩ ያ እንዳይሆን አቋም የወሰድንበት ጉዳይ ስለሆነ ጥያቄአችሁን ባለመቀበላችን ይቅርታ  እንጠይቃለን። ያም ቢሆን ለተሰደቡ ደጋፊዎቻችን ያለንን አድናቆት እየገለጽን የተሰደባችሁትና በሃሰት የተወነጀላችሁት እውነት በመናገራችሁ፤ ለመብት በመቆ ማችሁ በመሆኑ ልትኮሩ እንጂ ልታፍሩ አይገባችሁም እንላለን። እውነት የሆነውን ሁሉ ብንጽፍ ደግሞ በሃሰት  የተሰለፉትን ከስራ ማፈናቀል ይሆናል። ለመብት የቆሙ ደግሞ ጠንካሮች እንደሆኑ ማስረጃ የሚያስፈልግ አይሆንም። በየቀኑ የምታሳዩን እውነታ ነውና። እናንተን እያየን በየቀኑ እየተማርን ነው። መረዋ እውነትን ይዘው ከቆሙት ጎን በመቆሙ አሁንም ደስተኛ ነው። እውነት ለማሸነፉ ደግሞ ጥርጥር የለንም።

ዛሬ ከመረዋ  ከሰነበቱ እትሞች አለፍ አለፍ እያልን ልናስነብባችሁ እንወዳለን።ያለፈውን በማየት መጭውን ዳግም እንድናቃኝ ይረዳናልና።


ከመረዋ  ቁጥር ፩
11/26/09

"አሁን ለምን ሽማግሌዎች ሊያስታርቁ ተነሱ" ብሎ መተቸትና መሰናክል ለመፍጠር መነሳት ግን ሌላ ስህተት ነው ብለን ደግሞ እናምናለን። በፍርድ ቤት ትእዛዝ ችግራችን ይፈታል ብሎ የሚያምን ካለ የዋህ ነው ብሎ መናገር ማስፈራት የለበትም። ፍርድ ቤት በሚሰጠው ብያኔ ፍቅር አይመጣም አንድነት አይፈጠርም። ይህ ሊሆን የሚችለው የተለያየ ሃሳብ ይዞ የሚከራከረው ቡድን ተቀምጦ መነጋገር ሲችል ብቻ ነው። ክስ የመሰረቱትን ለምን ክስ መሰረቱ ብሎ መኮነን ደግሞ ሲደረግ የነበረውን መካድ ይህንን ባያደርጉ ኖሮ ዛሬ እንደዚህ ለመናገር የማንችልበት ሁኔታ ላይ እንሆን እንደነበር አለመቀበል ይሆናል። የቤተክርስቲያን ገንዘብ ስላለ ከሳሾቹን ገንዘባቸውን አስጨርሰን እንዲሸነፉ እናደርጋለን የሚሉት የቤተክርስቲያኑ ተመራጮች ማወቅ ያለባቸው ነገር ቢኖር የተመኩበት ገንዘብ ከምእመናን የተዋጣ መሆኑን ነው። ምእመኑ ካልደገፈ የገንዘቡ ቌት እንደሚሟጠጥ ከሳሾችንም ከአሁኑ በበለጠ እየደጎሙ እየደገፉ እንዲቀጥሉ ሊያበረታቱ እንደሚችሉ ማሰብም የተገባ ነው። ከሳሶችም ሆኑ የቤተክርስቲያኑ ተመራጮች ማወቅ ያለባቸው ነገር ቢኖር ያለ ምእመን ድጋፍ የትም ሊሄዱ እንደማይሄችሉ ነው። በተናጠል ቤተክርስቲያን አይገነባምና። ተሰዳደብን፡ ተካሰስን፡ ተወነጃጅለን አሁን ደግሞ ወደ አንድነት ለመምጣት ምን አስተዋጽኦ እናድርግ ብሎ መነሳት ክርስቲያናዊ ነውና ሁላችንም በተናጠል እራሳችንን ጠይቀን ለሰላም እንነሳ። እከሌን ብናገረው እንጣላለን ከመሃበር ያባርሩኛል ያልሆንኩትን ስም ይሰጡኛል፡ ዝምድናችን ይፈርሳል ጔደኝነታችን ይቀራል በቡድን ያጠቁኛል ብሎ በመፍራት ለእውነትና ለመብት አለመነሳት ደግሞ በሕሊና ማስጠየቅ ይኖርበታል እንላለን። ስለሆነም ለሁላችሁም ዛሬ ጥያቄዎች ማቅረብ እንወዳለን። በግል ምን እያደረግን ነው? ሰለኛ ሌሎች እስከመቼ ይወስናሉ?መብትና እምነት፡ ሕግና አምልኮን መለየት የምንችለው መቼ ነው?

ወንድሞችና እህቶች ይህ ከዚህ በላይ ያነበባችሁት መረዋ የመጀመሪያ እትምቱን ሲያወጣ የዘገበው ነው። እኛ ዛሬ ስናነበው የዛሬ ጽሑፍ መሰለን እናንተስ?

ከመረዋ  ቁጥር ፵፬ ደግሞ  እስቲ እናንብብ
10/06/10

 
ይህ ክስ አባላትን ማባረር ከጀመሩ በኋላ የተመሰረት መብትን ለማስከበር የተመሰረት ክስ መሆኑም ለሁላችንም ግልጽ ነው።
ስለሆነም በነገው እለት ምንም ተፈጠረ ምን
መተዳደሪያ ደንቡ ወደነበረበት ካልተመለሰ
የተባረሩ አባላት ካልተመለሱ
የአባላት ክፍያ ወደነበረበት ካልተመለሰ
አንዱ ልጅ ሌላው እንጀራ ልጅ መሆኑ ካልቀረ

የአባላት መብት ካልተጠበቀ
ፖለቲከኞች ከቤተክርስቲያን ውስጥ ፖለቲካቸውን ካላቆሙ
የምእመናንን ጥቅም አስከባሪ ቦርድ እስካልተቋቋመ
ብሎም
ባለፈው እንዳደረጉት ቦርዱ በመሰብሰቢያ አዳራሻቸው እነ አቶ ሃይሉ እጅጉን ጠርተው እየተሳደቡት ክስ ከመሰረቱት ውስጥ ነህና ካላረፍክ እንከስሃለን የክስ አጋሮችህንም አብረን ለፍርድ እናቆማለን እንዳሉት በተናጠል ማስፈራራት እስካላቆሙ ድረስ
በቦርዱ ብሎግ መሳደባቸውን እስካልገቱ ድረስ
መታገላችንን አናቆምም


አንዳዴ  ትላንት የተጻፉ ጽሑፎች ዛሬም እንዳዲስ የዛሬውን የሚተርኩ ይመስላሉ።

ይህንን ዳግም ልናስነብባችሁ የተነሳነው መረዋ ትላንትና የዘገበው ዛሬም እውነት መሆኑን ለአንባቢዎቻችን ለማስይረዳል ይጠቅማል ብለን በማሰብ ነው። ከሳሾች በስድብ አልደነበሩም። በማስፈራራት አልተበተኑም። በውሸት ወሬ አልበረገጉም። የሚንበረከኩት ለፍቅር፤ ለእውነት ለመሆኑ ደግሞ ጥርጥር የለንም። ይህንንም በተደጋጋሚ ሊያወያዩ ለተነሱ አዛውንቶች ሁሉ ያረጋገጡት ለመሆኑ መስካሪዎቹ አዛውንቶቹ ይሆናሉ እንላለን። በመወያየት የሚያምኑት የከሳሽ ወገኖች የሚያሸንፉትም ሆነ የሚሸነፉት በውይይት ብቻ እንደሆነ ያምናሉ። ለካሳ አልተነሱም፡ ለመብት መከበር እንጂ። አማንያንን ለመበታተን አልተነሱም የተበተነውን ለመሰብሰብ እንጂ። ለመከፋፈል አልተነሱም አንድነትን ለመፍጠር እንጂ። ይህ ደግሞ ሊመጣ የሚችለው በመነጋገር ብቻ እንደሆነ  ጥርጣሬ  የላቸውም።   የመነጋገር በሩ ከተዘጋ ግን አማራጩ አንድ ብቻ ይሆናል። መብትን በፍርድ ቤት ማስከበር ብቻ። ይህ ሳይሆን ክሱን ተው ብሎ መጠየቅ ግን "ታንክ ከያዘ ጠላት ፊት ቡጢ ይዛችሁ ቅረቡ" እንደ ማለት  ይመስላል።
ከሳሽ የምንላቸው ግለሰቦች ገንዘባቸውንና ጊዜአቸውን የማባከን ሱስ የለባቸውም። ለመብታቸው ትግል ባይጀምሩ ኖሮ ግን እንደማይሰደቡም ያውቃሉ። እንደ ቦርድ አባላት በ ሺ የሚቆጠር እንደፈለጉት የሚያጠፉት የባንክ ደብተርም የላቸውም። ከደጋፊዎች የሚሰበሰብ የድጋፍ መዋጮ እንጂ። ታዲያ የሚያገኙት ምንድነው ለሚሉ ግለሰቦች መልሱ መብታቸውን ማስከበ ይሆናል። ትላንት ፍርድ ቤት ባይሄዱ ኖሮ   81 የቤተክርስቲያን አባላት ከቤተክርስቲያን በፖሊስ ተባረው ነበር። ፍርድ ቤት ባይሄዱ ኖሮ ቤተክርስቲያን ለአምልኮ እንኳን እንዳይደርሱ ተከልክለው ነበር። ይህንን እንዳያደርጉ በፍርድ ቤት ሲታዘዙ አይደለም እንዴ የቦርድ አባላት ይግባኝ ብለው ዛሬም የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤትን ውሳኔ በጉጉት የሚጠብቁት። ለምን እንደባበቃለን። ከሳሾች አባላት አይደሉም አናውቃቸውም ያሉት የቦርድ አባላት አይደሉምን?ለምን እንደባበቃለን። ከሳሾች የጀርመን ናዚ ፋሽስት የወጣት አባላት አይነት ናቸው ብለው ለፍርድ ቤት ቃላቸውን የሰጡት አሁንም የቦርዱ አባላት አይደሉምን?
ለምን እንደብቃለን? ከሳሾች ልጆች እንደሌላቸው ሁሉ፣ ሕጻናቶችን ከጫማ ጋር ከፎቅ ላይ ወደ መሬት ሊወረውሩ ነበር ተብለው በፍርድቤት አልተወነጀሉምን? ይኸ ልክ አይደለም ያሉ ሁሉ ከሳሾችን ለመርዳት ቃል እንዲገቡ አደረጋቸው እንጂ እነሱ እንዳሰቡት ደጋፊ አላሳጣቸውም። የቦርድ ደጋፊ ነን ባይ ጦማርም "they are  inocent till they are prooven  gilty"  ሲሉ አላዳመጥንም። ብቻ  ሆድ ይፍጀው። አገሩ ደግሞ  የዲሞክራሲና  የመብት አገር የሕግ የበላይነት ያለበት ምድር መሆኑ እረዳን።

ይህንን በዚህ እናጣፋና ወደ ሌላ ጉዳይ እንግባ

ከዚህ በፊት በደረሰው በወጣቱ ሐዘን ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተላልፎ የነበረው የተባበሩት የሰላምና ፍትሕ አስተባባሪ ኮሚቴ  አጠቃላይ ስብሰባ እሁድ
January  23, 2011 ከቀኑ 1:00 PM
በ DREAMZ CLUB 
እንደሚደረግ የደረሰን ማሳሰቢያ ይገልጻል። በወቅቱ ከስብሰባው በፊት ምሳ  እንደሚኖርም ለመረዳት ችለናል።

ሳንረሳው መጥቀስ የምንወደው ሌላ ጉዳይ አለ። ሰሞኑን በሌላው ጦማር እንደ ተለመደው በአቶ ተኮላ መኮንን ላይ የተሰነዘረውን የሃሰት ውንጀላ አስመልክቶ የተጻፉ መልሶች

 በ WWW.ASSIMBA.COM

እየተለጠፉ እንደሆነ መገንዘባችንን ለአንባቢዎቻችን እንገልጻለን።



የከርሞ ሰው ይበለን።