Tuesday, February 22, 2011

የፍርድ ቤቱ ቀጠሮ

ውድ አንባብያን እንዴት ከረማች? እኛ አሁንም የጀመርነውን ለመጨረስ ከመታገል ወደ ኋላ አላልንም። የተፈጠረ ብዙ ነገር ብንታዘብም የፍርድ ቤት ዜና ከማግኘታችን በፊት ለእትምት ላለመውጣት ወስነን ነበርና ይህንኑ ስንጠብቅ ሰነበትን። እነሆኝ በዛሬው እለት የደረሰን ዜና እንደሚጠቁመው ባለፈው ተላልፎ  የነበረው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ለ March 23, 2011 9:30 AM መቀጠሩንና ሁላችሁም መጋበዛችሁን መረዋ ማሳሰብ ይወዳል። ስለሆነም በተባለው ቀን ፍርድ ቤት ለመገኘት ካሁኑ የስራ እቅዳችሁን  እንድታስተካክሉ በድጋሜ  እናሳስባችኋለን። 

በተጨማሪ ከማንም ያልወገነ ገለልተኛ የተባለው ቤተክርስቲያናችን የአመራር አባላትና ካህናት ባለፈው ሳምንት ወደ ሂውስተን በመጓዝ ከስደት ሲኖዶስ አባቶች ጋር መገናኘታቸውን የደረሰን ዜና  ይጠቁማል። በወቅቱ በስፍራው  ተገኝተው የነበሩት አባ መልከጸዴቅ የዳላስ ሚካኤልን ወደ ስደት ሲኖዶስ መጥቶ  የቤተክርስቲያኑ አመራሮ ች በመሃከል መገኘታቸውን ከማብሰራቸውም በላይ ከዚህ በፊትም 7 ዲያቆናትን የስደቱ ሲኖዶስ ድቁና  መስጠቱን አውስተዋል። በመቀጠልም ከኮሎምቦስ የስደት ሲኖዶሱ ካህን ወደ  ዳላስ ተልከው በስራ  ላይ እንደሆኑም መጠቆማቸውን የደረሰን ዜና  ያረጋግጣል። የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ዘማርያንም የቤተክርስቲያኑን አልባሰ መዘምራን አጥልቀው ይዘምሩ እንደነበርም ለማረጋገጥ  ችለናል።

ገለልተኛ የተባለው ይህ ቤተክርስቲያናችን ማንንም ሲኖዶስ አንደግፍም ሲባል ቆይቶ ዛሬ የቦርድ አባላት በእንግድነት ከነባለቦቶቻቸው መገኘት ብቻ  አይደለም መዘመር ከቻሉ ገለልታኛነቱ እምኑ ላይ እንደሆነ እራሳችሁ እንድትጠይቁ ለናንተ  እያቀረብን መረዋ  ከዓመት በፊት ያነሳው የቦርድ አባላት እቅድ እየተፈጸመ  መሆኑን ከመታዘብ በስተቀር አልተደነቅንም። ትላንትናም ሆነ  ዛሬ ትግሉ ቤተክርስቲያኑን ተቆጣጥሮ የፖለቲካ ዓላማ  መጠቀሚያ ለማድረግ እንደሆነ የምናውቀው ነገር ፣ የተናገርነው ነገር ነበር። ትላንት ውሸት ተብለን ነበር ዛሬ  ምን እንባል ይሆን?

የወር ሰው ይበለን?

የመብት ትግላችን ይቀጥላል።

Wednesday, February 9, 2011

ዘግይቶ የደረሰን

እንዴት ሰነበታችሁ ውድ አንባብያን

ባለፈው እትምታችን እንደነገርናችሁ ተከሳሽ የሆኑት የቤተክርስቲያኑ የቦርድ ባለስልጣናት ቀደም ባለው ዳኛ ተወስኖ የነበረውን

በመቅደስ ውስጥ ፖሊስ አታስገቡ
አማንያንን አታባሩ
መዛግብቶችንና የኮሚፒውተር መረጃዎችን እንዳታጠፉ ብሎ የወሰነባቸውን በመቃወም ይግባኝ  ማለታቸው የሚታወስ ነው። በመሆኑም በ2 / 7/ 2011 ያስቻለው የይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት በከሳሽና  በተከሳሾች ጠበቆች የቀረበውን የቃል ክርክር አዳምጠዋል። በወቅቱ የተሰየሙት 3 ዳኞችም ለሁለቱም ጠበቆች  እንዲብራራላቸው የፈለጉትን ጥያቄዎችም ጠይቀው መልሱን  አዳምጣዋል።

ከሳሾችን አናውቃቸውም ያሉት የተከሳሾች ጠበቃ ከሳሾች ማክዶናልድ  ምግብ ቤት ሃምበርገር ተመላልሰው በመበላታቸው የማክዶናል የቦርድ አሰራር አላማረንምና የመቀየር መብት አለን እንደሚል ግለሰብ ናቸው ብለዋል። ስለሆነም እኛም ያልመሰለንን  የማስዋጣት የማባረር መብታችን መጠበቅ አለበት ምክንያቱም ቤተክርስቲያን በመሆናችን  መንግስት ጣልቃ  ሊገባብን አይችልም መንግስት መግባት የሚችለው የንብረት ይገባኛል ጥያቄ ይዘው ቢቀርቡ ነበር  ማለታቸውን ለመረዳት ችለናል።
የከሳሾች ጠበቃ በበኩላቸው እነዚህ ተመራጮች ያላግባብ የተመረጡ ከመሆናቸውም በላይ ጥያቄ ተጠየቅን ብለው ሴትና ሕጻናት በተሰበሰቡበት ወገን ፖሊስ እያስገቡ ያሳሰሩ ብሎም መብታቸውን በመጠቀም አባላትን ለማባረር የተነሱ መሆ ናቸውን አውስተው ጉዳዩ የእምነት ሳይሆን የመብት መገፈፍ መሆኑን አስረድተዋል። በ2/10/2011 ዳኛ ስሚዝ በይግባኝ ሰሚነት የሚያዩት ለውሳኔ  የቀረበ  መዝገብ እንዲያሳዩ  በበታች ዳኛ  የተወሰነውን አሻፈረን በማለት አሁንም የቦርዶቹ ጠበቃ ያቀረበው ስለለ የእሱንም ውጤት የይግባኝ  ሰሚው ፍርድ ቤት መጠበቅ ይኖ ርበታል ብለዋል።
ፍርድ ቤቱ የቀኑን የጠበቆች ገላጻ አዳምጦ የእለቱ ሸንጎ ፍጻሜ  ሆኖ ተበትኗል።




ዘግይቶ  የደረሰን ዜና በነገው እለት 2/10/2011 ተቀጥሮ  የነበረው ይህ ቀጠሮ በከሳሾች ጠበቃና በዳኛው የፕሮግራም መጋጨት መተላለፉን ለመረዳት ችለናል።  የቀጠሮውን ቀን እንደደረሰን ለአንባብያን እናስታውቃለን።

የከርሞ  ሰው ይበለን።