Wednesday, March 23, 2011

የዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ

እንደምን ከረማችሁ ምእመናን

የተለየ ነገር ሳይኖር በተደጋጋሚ እናደርገው እንደ ነበረው በተከታታይ ባለመውጣታችን ምን ነካችሁ?  ላላችሁን። መረዋን አትግደሉብን ብላችሁ ለጠየቃችሁን። መረዋ ላይ ካልወጣ እውነት አይደለም ላላችሁና እምነት ለጣላችሁብን ሁሉ ምስጋናችን ወሰን የለውም። ዋሽተን ከምንከበር ይልቅ እውነቱን ተናግረን ብንወገር እንደምንመርጥ መናገር ደግሞ እውነትነቱ አንደማያጠራጥር ምስክሮቻችን እናንተ  ናችሁ።  በመሆኑም እንደ ተለመደው የዛሬን  የፍርድ ቤት   ውሎ እናካፍላችሁ። 

ባለፈው እትምታችን እንደ ነገርናችሁ  የዛሬው ቀጠሮ በ 192 የካውንቲ ችሎት በዳኛ ስሚዝ ፊት የተደረገ ክርከር ነበር። ባለፈው እረዳት ዳኛ የቦርዱ ሹማምንት ከከሳሾች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን የመመለስ ብሎም የቤተክርስቲያኑን ዶሴዎች የማሳየት ግዴታ አለባችሁ ብለው የወሰኑትን ውሳኔ በመቃወም የቦርዶቹ ጠበቃ  ለዋናው ዳኛ ስሚዝ ይግባኝ ማለታቸው ይታወሳል። የዛሬው ቀጠሮ ከመድረሱ በፊት ባለፈው በቦርዱ ላይ ተጥሎ የነበረውን እገዳ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እንዳነሳላቸው የዘገብነው ጉዳይ ነው።

በዛሬው  እለት የተከሳሾች ጠበቃ ለፍርድ ቤቱ በ march 21st ያስገቡት  ማመልከቻ ለከሳሾች ጠበቃ እንዳልደረሳቸው ለፍርድ  ቤቱ ሲናገሩ ፍርድ ቤቱ ለምን? ብሎ  የተከሳሾችን ጠበቃ  ሲጠይቅ መልሳቸው በfax ልከናል የሚል  ነበር። ፋክስም እንዳልደረሳቸው የተናገሩት የከሳሾች ጠበቃ ባላዩት ማመልከቻ  ላይ ምንም ውሳኔ  ሊሰጥ  እንደማይቻል ተናግረው ዳኛው ተስማምተዋል። ዳኛው የይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት በሃይማኖት ጣልቃ  አትግቡ ብሏልና ለምን ጉዳዩን አየዋለሁ? ብለው ለጠየቁት ጥያቄ የተከሳሾች ጠበቃ  እኛም የምንለው እሱን ነው ብለው ሲመልሱ፣ የከሳሾች ጠበቅ ግን የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የወሰነው በእገዳው ላይ እንጂ በክሱ ይዘት ላይ አይደለም በማለት ተከረክረው ለዚህም በውሳኔው መደምደሚያ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን 
ፍሬ ሃሳብ ሳይተችበት ለዳኛ ስሚዝ ማስተላለፉን ጠቅሰዋል። የከሳሾች ጠበቃ  አያይዘውም አሁንም ቢሆን በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ አልስማማም ያ  እንዳለ  ሆኖ ለክቡር ፍርድ ቤቱ ልጠይቅ የምፈልገው እነዚህ የቦርድ አባላት እንደ ፈለጉ ሕግ መቀየር ከቻሉ ነገ  አዲስ ሕግ አውጥተው ንብረቱን ወስደው ቤተክርስቲያኑን ሸጠው ወደ ጃማይካ  ቢሄዱ ምን የሚያግዳቸው ነገር አለ። እዚህ ቤተክርስቲያን አባል መሆን ለምን ያስፈልጋል?  ፈላጭ ቆራጩ ቦርድ እንጂ አባላት ምንም መብት የላቸውም። የከሰሰ  ከአባልነት ይባረራል ካሉ። አባል ለመሆን ማመልከቻ  አስገብቶ  የቦርዱን ፈቃድ መጠየቅ ካለበት ስልጣኑ የምእመናን ሳይሆን የቦርዱ ነው ብለዋል። ስለሆነም ቦርዱ ነገ  ሕጉን  ቀይሮ ምንም ማድረግ ይችላል አባል ምንም መብት የለውም ብለው ለፍርድ ቤቱ አሳስበዋል። በተጨማሪም ይህ ቤተክርስቲያን የ  501 C ፈቃድ ያለው እስከ ሆነ ድረስ  የፌድራልና የስቴት ሕግ የመከተል ግዴታ  አለበት በሃይማኖት ሽፋን ወንጀል መስራት አይችሉም ብለዋል። የተከሰሱት የቦርድ አባላት የራሳቸውን ሕግ እንኳን የማያከብሩ ናቸው ለዚህም የምርጫቸውን ሁኔታ መመልከት ይቻላል በማለት ተከራክረዋል። የተከሳሾች ጠበቃ የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ከወሰነው ውጭ ፍርድ ቤቱ ምንም ማድረግ አይችልም ብለው ዛሬውኑ ክሱ ተሰርዞልን እንሰናበት ብለው ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ነበር።

በመጨረሻም ዳኛው ሁለቱ ጠበቆች ተስማምተው የመከራከሪያና  የፍርድ ሃሳባቸውን ከዚህ በፊት ከነበሩ ተመሳሳይ  የተለያዩ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ጋር እንዲያቀርቡላቸው ሁለት ሳምንት ሲሰጡ ስምምነቱን አስመልክቶ የተከሳሽ ጠበቃ ጽፈውና ፈርመው ለከሳች ጠበቃ እንዲያሳልፉ የከሳሽ ጠበቃ ደግሞ ፈርመው ለፍርድ ቤቱ እንዲያቀረቡ ነግረዋቸዋል።

ዳኛው የሁለቱን መከራከሪያ ነጥብና የፍርድ ሃሳብ ካዩ በኋላ ማስረጃ መስማት እንደሚያስፈልግም ሆነ ክርክሩን ለመክፈት ወይንም ለመዝጋት ውሳኔ  ለመስጠት ለ APRIL 15 ቀጠሮ  ሰጥተው የእለቱ ችሎት  ተፈጽሟል።

በተጨማሪም በወይዘሮ ጥሩአየር እና  በአቶ  ዳግም ከሳሽነት ተመስርቶ በዳኛ  እስሚዝ የቦርዱ አባላት ካለ አባላት ፈቃድ ሕጉን መቀየር ይችላሉ ብለው የበየኑት ብያኔ  የሚታወስ ነው። ውሳኔውን በመቃወም ከሳሾቹ ለይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ይግባኝ  ማለታቸው ይታወሳል። ስለሆነም ጉዳዩን በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እያለ ከሳሾች ፍርድ ቤቱ ያለውን መረጃ ተመልክቶ  ውሳኔ  ይስጠን ቢሉም የቦርዱ ጠበቆች የለም የቃል ክርክር እንፈልጋለን በማለታቸው የቃል ክርክሩን ለማዳመጥ ጉዳዩ ለመጭው MAY 4, 2011 
ሰዓት 1:00PM  
ላይ መቀጠሩን ልንነግራችሁ እንወዳለን።
ቦታው 600 COMMERCE # 200
COURT OF APILE
FIFTH DISTRICT OF TEXAS


ማንኛውም የቤተክርስቲያን ምእመን በፍርድ ቤት በመገኘት ክርክሩን ማዳመጥ  እንደሚችል ስንነግራችሁ በደሰታ  ነው።
የቦርድ አባላት የማያልቅ ገንዘብ ስላላቸው ብዙ የማቆያ ዘዴዎችን እንደሚጠቀሙ ትላንት ፍርድ ቤት የተነገረ ሲሆን፣ መብታቸው የተደፈረው ምእመናን ደግሞ  ፈጣሪንና ደጋፊዎቻቸውን ይዘው መታገላቸውን እንደማያቆሙ ከሂደቱ መገንዘብ ይቻላል።

መረዋ ለምእመናን የሚጠይቀው ነገር ቢኖር መብት የሌለው አባልነት ምንድነው? የሚል ይሆናል።

መረዋም የዛሬውን ዘገባ  በዚሁ ያበቃል።

Friday, March 4, 2011

ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሰጠ

ውድ አንባብያን እንደምን ከረማችሁ

ባለፈው የቦርድ አባላት ግለሰቦችን ከቤተክርስቲያን እንዳያባርሩ ዶሴዎችን እንዳያጠፉ ተጥሎባቸው የነበረውን እገዳ በመቃወም ይግባኝ  ማለታቸው የሚታወስ ነው። በትላንትናው እለት ጉዳዩን የሰማው ፍርድ ቤት ዳኛው አስቀምጦት የነበረውን እገዳ  በማንሳት ክርክሩን ወደሚያዳምጡት ዳኛ መልሶ  መላኩን ለመረዳት ችለናል።   

በዳኞቹ አባባል የመታደደሪያ  ደንቡ ማንንም ሰው ቤተክርስቲያን እንዳይመጣ ቁርባን እንዳይቀበል ቦርዱ መከልከል አይችልም የሚለውን ይህ በውሰጥ ሊፈታ የሚችል በመሆኑ ፍርድ ቤት ማዘዝ አይችልም ብለው  ሲወስኑ የጉዳዩን ጭብጥ ክርክር ግን አናይም በማለት ውሳኔው እገዳውን በተመለከት ላይ ብቻ ያተኮረ መሆኑን ጠቅሰው ሁኔታውን እንዲያዩትና ክርክሩን እንዲሰሙ ለዳኛ ስሚዝ ዶሴውን መልሰው መላካቸውን ጠቅሰዋል።

ገንዘብ እንዳያባክኑ  ዶሴዎችን እንዳያጠፉ ተጥሎ  የነበረውን እገዳ ዳኞቹ ቦርዱ ገንዘብ ለማባከኑና  ዶሴዎችን ለማጥፋቱ የቀረበ  መረጃ ባለመኖሩ እገዳውን አንስተንዋል ሲሉ  ወደፊት ግን ይህ ለመደረጉ መረጃ  መስማት እንዲችሉ ለዳኛ ስሚዝ ጉዳዩን ክፍት በማድረግ ትተውታል።

ይህንን  አስመልክቶ  ሊቀርብ የሚችል ብዙ መረጃ  መኖሩን ስለምናውቅ የሚያስጨንቅ አለመሆኑን ለአንባብያን መናገር እንወዳለን። እስካሁን ምንም ክርክር ሳይጀመር ምስክር መስማት ሳይቻል  በአሰራር ብቻ  እየተወሰነ  ያለውን ጉዳይ አለቀ የሚሉ ካሉ ትልቅ ስህተተ  እየተሳሳቱ እንደሆነም መናገር እውነት ይሆናል።

የይግባኝ ፍርድ ቤቱ በእገዳው ላይ ብቻ ውሳኔ መስጠታቸውን ተናግረው ክሱን አስመልክቶ ምንም ውሳኔ አለመስጠታቸውን አስፍረዋል። ይህንን  ማድረግ የሚችሉት ዳኛ ስሚዝ እንደሆኑም ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።  ለዚህም ነው ዶሴው ወደሳቸው ፍርድ ቤቱ የተመለሰው።

በ3/23/2011 9:15 AM

በዳኛ ስሚዝ ችሎት እንድንገናኝ ጥሪ እያቀረብን  ለዛሬው በዚሁ እንሰናበታችኋለን።

ክርክሩ ተጀመረ  እንጂ አላለቀም።