Wednesday, August 25, 2010

ትልቅ ሰው በምሳሌ ያስተምራል ቀላል ሰው በስድብ ያርቃል። ቁጥር ፵

መጽሐፍ ቅዱስ አገላበጥንና "የሚሳደቡ ብጹአን ናቸው መንገስተ ሰማያትን ይወርሳሉና "የሚል ጥቅስ ማግኘት ግን ተሳነን። የሚሳደብ ሰው የሃሳብ ድሃ የሆነ ብቻ ነው።  ባለጌ ባለጌ መሆኑን የምታውቀው በግብሩና በምላሱ ነው ይባል ነበርና። ግለሰብን በማዋረድ እናቶችን በመዝለፍ፤ በታመሙ በመቀለድ፤ በሙት ላይ በማፌዝ:የግለሰብን ስም እየጠቀሱ በማስፈራራት ትልቅነት አለ ከተባለ ትልቆቹ እነማን እንደሆኑ ደግሞ እያወቅን እየመጣን ያለን ይመስለናል። ዝም ያለ ሁሉ የፈራ የሚመስላቸው፤ የመናገር እንጂ የማዳመጥ ባህሉም ልማዱም እውቀቱም የሌላቸው ግለሰቦች ብቻ ናቸው። የሚጽፉትን በማየት ደረጃቸውን ለመለየት ደግሞበነሱ አባባል " የመንኮራኩር ፈላስፋ"መሆንን አይጠየቀምና።

ውድ አንባብያን

በፍርድ ቤት የተያዘው የይግባኝ ጉዳይ የመልስ መልስ ተሰጥቶት በቅርቡ ውሳኔውን  እየተጠበቀ መሆኑን የተቆርቌሪዎች ቡድን አባላት አብስረውናል። በስድብ የተካነውና ግለሰቦችን እያዋረደ፡ ያለው የቦርዱ ደጋፊ ነን ባዮች ድሕረ ገጽ ለከሳሾቹ ክስ መልካም መረጃን እያቀበለ ለመሆኑ በቅርቡ የምናየው ታላቅ የምስራች እንደሚኖር መረዋ ለአንባብያን መናገር ይወዳል። የማስፈራሪያና የስድብ ምንጭ የሆነው ይህ ድሕረ ገጽ የመናገር መብትን የጣሰ፤ የግለሰብን መብት የተጋፋ፤ ከመጋረጃ ኋላ  ተደብቆ ግለሰቦችን የሚያስፈራራና የብዙዎችን የመሥራት፤ የመንቀሳቀስ መብት የሚጋፋ ከመሆን አልፎ የሰው ሕይወት እንዲጠፋ  ቅስቀሳ  የሚያደርግ ለመሆኑ በተደጋጋሚ ያወጣቸው ጽሁፎችን ተንተርሶ ለፍርድ የሚቀርቡበት ሰዓት መቃረቡን ስንናገር፤ ለመብት የታገለ  ማንኛቸውም ግለሰብ ይህንንም የመታገል ግዴታ  እንዳለበት በማሳሰብ ጭምር ነው።

ማንም ግለሰብ ቤተሰቡንና ንብረቱን ብሎም እራሱን የመከላከል ሙሉ መብት እንዳለው ሁሉ፤ መንግሥትም የግለሰቦች ሕይወት አስጊ ደረጃ ላይ ሆኖ  ሲያገኘው የመከላለልና የዜጎችን መብታቸውን የመጠበቅ ሃላፊነት አለበት። በደል ሲደርስ ወደ ሕግ መሄድ አዋቂነት እንጂ የሚያሰድብ ብሎም ያልተደረገ ፈጥሮ  ስም የሚያስጠፋ  መሆን አይኖርበትም።  ማንም ከሕግ በላይ መሆን አይቻለውም። የግለሰብ መብት የሚከበረው የሌላውን መብት እስካልተጣሰ  ድረስ ብቻ ነው።  ስለሆነም በሚጻፈው የተደናገጣችሁ የቤተሰቦቻችሁና የራሳችሁ ሕይወት አስጊ ደረጃ ላይ ነው ብላችሁ የምታስቡ ሁሉ፡ ድርጊቱ ከመፈጸሙ በፊት ወደ ሕግ እየሄዳችሁ ለሕግ አስከባሪዎች ማሳወቁ ለተጀመረው እንቅስቃሴ እነደሚረዳ ልናሳስባችሁ እንወዳለን። የሕግ የበላይነት እንደሚያሸንፍ ደግሞ ምንም ጥርጥር የለንም።  

ይህንን በዚህ እናቁምና ባለፈው እሑድ የቤተክርስቲያኑን መኪና አሽከርክሮ ወደ ሂውስተን ሄዶ የነበረው የቦርዱ ተወካዮችና የእናቶች የዘማሪ ቡድን አባላት እንደተጠበቀው ከስደት ሲኖዶስ ከመጡት አራት ተወካዮች ጋር ተገናኝቶ መምጣቱንና 5 ልጆችም ከዚሁ ከስደቱ ሲኖዶስ የድቁና ማእረግ ተቀብለው መምጣታቸውን የደረሰን ዜና ያረጋግጣል። ድቁና ከተቀበሉት መሃል ሁለቱ የቦርድ አባላት ልጆች አንደኛው ለቦርዱ የመከላከያ ምስክር የነበሩት "ሕፃናትን ከፎቅ ሊወረውሩ ሲማከሩ ሰምቻለሁ" ብለው የመሰከሩት ግለሰብ ልጅ መሆናቸውን ሁኔታውን የተከታተሉት ምእመናን አውስተውናል። "የስደት ሲኖዶስን ለማምጣት የተጀመረው ትግል ፍሬ እያገኘልን ነው" የሚሉ የስደት ሲኖዶስ አላሚዎች የፖለቲካ  ድርጅቶችና ግለሰቦች ፈገግታ ቢያሳዩ እውነታ አላቸው። መረዋ  የተጻራሪዎች ትግላቸው ይህን እቅድ በሥራ ለመተግበር እንደሆነ የተናገረበት ሰዓት ውሎ ስላደረ ነግረናል ከማለት በስተቀር አልተገረምንም።

ባለፈው እሁድ በቤተክርስቲያኑ የሰበካ  ሰዓት ከባለቤቷ የተጣላች እናት ወደ ሃገር ቤት ለመላኪያ ገንዘብ አዋጡ ተብሎ ገንዘብ በመዋጣት ላይ እንዳለ ከመሃል ተነስተው "ቤተክርስቲያን አስታራቂ እንጂ አፋቺ የሆነችው መቼ ነው?" ብለው የጠየቁት እናት ጥያቄአቸው ትክክል እንደነበረ ብንገነዘብም ወዲያው የዘር ግንዳቸውን ዳሰው የተለመደ የስድብ ውርጅብኝ እንዳያወርዱባቸው ፈርተንላቸው ነበር። ነገር ግን ያካባቢው ሰፈርና የቤተክርስቲያኑ መብራት በመጥፋቱ በቶሎ ለመበተን ችለናል።መብራቱን ያጠፉት ደግሞ የከሳሽ ቡድኖች ናቸው ተብሎ መወንጀሉንም በብሎጋቸው ላይ ያነበባችሁት ጉዳይ ነው።  "የመቀበር መብታችንን የሚገፍ መንግስት ባገራችን ጣለብን" ያሉት የእለቱ አስተማሪ ካህን ከፖለቲካው ውስጥ ባይገቡ ኖሮ ትምህርታቸው መልካም ነበር። ነገር ግን የከበቧቸውን ፖለቲከኞች አስደስታለሁ ብለው ያልሆነ ስህተት ፈጸሙ ብሎ መናገር  ለወደፊቱ ትምህርት ይሆናቸዋል ብለን እናምናለን።

ውድ ወንድሞችና እህቶች

ክርስቲያን በእምነት ላይ የተመረኮዘ እንጂ በዘር የተገነባ ከሆነ መጥፎ ለመሆኑ መስካሪ አያስፈልግም።

በአንድ ወቅት ሁለት አፍሪካ አሜሪካውያንን ያየ የአራት አመት ልጅ ለእናቱ  "mommy look this N......"
ሲል እናትየዋ የተሰበሰበውን ሰው ተመልክታ   " I am sorry" ብላ መለሰች።
ይህንን የሰማ አንደኛው አፍሪካ አሜሪካዊ  "don't worry we will credit  it to the source" 
ያለውን ያጫወተን ቀልደኛው ጔደኛችን ነበር።
አይዞሽ አትጨነቂ ለህፃኑ ይህንን ማን እንደነገረው እናውቀዋለን ማለቱ ነው። በሌላ  አባባል የተማረው ካንቺ ነው ብሎ ለማለት ነው።

ልጆቹን  የሚበላ ለድሮ ድመት ወይም ውሻ ብቻ ነበር ዛሬ ግን ክርስቲያን ነን የሚሉ ሲያደርጉት ስናይ አዘንን። በውሸት ፍቅር ይመጣ ይመስል የስድብ ውርጅብኝ እያወረዱ መደምደሚያው ላይ "ወደ ክርስቶስ ቤት ተቀላቀሉ" የሚሉ ያስቁናል። እራሳቸውን እንዳታለሉ ሁሉ ፈጣሪንም ያታለሉ እንደሚመስላቸው ግብዝነታቸውን በማየታችን።

ሌላው ሳናነሳው የማናልፈው ባለፈው በምእመናን የተቌቌመውን የምእመናን እንባ አስጠባቂ ኮሚቴ አባላት ስም ዝርዝር እንዲሁ በድሕረ ገጽ ላይ ወጥቶ ተመልክተናል። ለነገሩ ይህ ባደባባይ ሕዝብ ተሰብስቦ የተቌቌመ  ኮሚቴ እንጂ የሕቡእ ኮሚቴ ባለመሆኑ የስም ዝርዝሩም እንዲሁ ያደባባይ ሚስጥር ነው። ኮሚቴዎቹ በሥራ  እየተፈተኑ ለመሄድ የተዋቀሩ መሆናቸውን እንደ እንጉዳይ የሚጠፉ ሳይሆን እንደድር የተሳሰሩ መንፈሰ ጠንካሮች መሆናቸውን ከተመለከነው መናገር እንወዳለን። "ለደህና እቃ ማስታወቂያ  አያስፈልገውም" እንዲሉ በሥራችን እንጂ በስማችን መኩራራት አይኖርብንም ብለው ያለፉትን እናንተ መተዋወቅ አለባችሁ ካላችኋቸው ለጥረታችሁ እናመሰግናለን ብለው ያመሰብኑ ካልሆነ በስተቀር "ውይ ሥማችን ወጣ ብለው እንደማያፍሩ: አንጠራጠርም። በሚሰሩትየስራ ውጤት ደግሞ  እንደምታፍሩ ቃል  ብንገባ ካየነው በመነሳት ነውና ውሸት አይሆንም።
በሚቀጥለው እትምታችን በትልቅ ዜና እንደምንገናኝ በቅድሚያ ቃል እየገባን ለዛሬው በዚሁ እንሰናበታለን።

በነገራችን ላይ ለማንኛውም በ E MAIL ልትገናኙን ለምትፈልጉ ሁሉ አድራሻችን

yetayalewnetu@gmail.com   ነው


የከርሞ  ሰው ይበለን

ቸር ወሬ ያሰማን።

Monday, August 9, 2010

ከምእመናን የደረሰን ዜና ቁጥር ፴፱

ላለፉት ወራቶች በቤተክርስቲያናችን የተፈጠረው ችግር አሳስቦአቸው መፍትሄ  ማግኘት አለብን ብለው የተነሱት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አባላት በቤተክርስቲያኑ አዳራሽ ለመሰብሰብ መከልከላቸው ሳያናድዳቸው የሆቴል አዳራሽ ተከራይተው "የተባበሩት የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የመፍትሄ ኮሚቴ"  ማቌቋማቸው የሚታወስ ነው። ይህ በጅምሩ የ200 አባላትን የሥም ዝርዝር ይዞ የተዋቀረው ኮሚቴ የደጋፊዎቹ ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መሄዱን በመግለጽ በሃላፊነት የተቀበለውን ሥራ ለማቀላጠፍ ይረዳ ዘንድ በትላንትናው ስብሰባው የተለያየ ኮሜቴ ማዋቀር አስፈላጊ ሆኖ  ስላገኘው  9 ኙ የኮሚቴ አባላት በተዋረድ የሚሳተፉበት 4 ኮሚቴዎች ማቌቌማቸውን ከስፍራው የተገኙ ምእመናን ገልጸውልናል።

በእለቱ በተደረገው የኮሚቴ ማዋቀር ስብሰባ ላይ እንደተነገረው አባላት ምነው ዘገያችሁ? ማለታቸው የተገባ  ጥያቄ  መሆኑን የዘገቡት የኮሚቴው ሰብሳቢ "ጥልን ለማፋፋም እንጂ ሰላምን ለመፍጠር  ጊዜ  እንደሚፈጅ መታወቅ እንዳለበት ጠቅሰው በተለያየ መልኩ ግን ብዙ በይፋ ያልወጡ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑንና በተለይም ባለፈው ወር በግለሰብ ተጠርቶ በነበረ ውይይት ላይ በመገኘት ከተላያዩ ጉዳዩ ይመለከተናል ከሚሉ የቤተክርስቲያን  አባላት ጋር ውይይት ኮሚቴው ማድረጉን " ለተሰብሳቢዎቹ ገለጻ አድርገዋል"። ይህ ዛሬ የተቋቋመው ኮሚቴ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አለመሆኑን የተናገሩት ሰብሳቢ በኮሚቴው ውስጥ ገብቼ  ለማገልገል እፈልጋለሁ ለሚል ለማንም ኢትዮጵያዊ በሩ ክፍት መሆኑን ጠቅሰው፡ አሁንም መፍትሄ የምናመጣው ተሰብሰቦ በመነጋገርና በመወያየት  መሆን አለበት ብሎ ስብስቡ  እንደሚያምንና በዚህም መርህ እንደሚመራ ጠቅሰዋል። በአሁኑ ወቅት የሰላም መንገዱ የተዘጋ በመሆኑ ደግሞ የሕግን የበላይነት በሕግ ማስከበረ አማራጭ የሌለው መንገድ ሆኖ መገኘቱን ለተሰብሳቢው አስረድተዋል።

በእለቱ የተሰበሰቡት የኮሚቴ ተመራጮች ስራቸውን ለማከናወን እንዲራዳቸው በጸሎት የከፈቱት የመንፈሳዊ አባቶች የራሳቸው ችግር ሳይሆን የምእመናን መበታተን እያስፈራቸው እንደሆነ  ጠቅሰው ክርስቲያን ሽንፈትን የሚቀበል ሳይሆን ጥንካሬን የሚያስተምር መሆን አለበት ብለው ለተሰብሳቢዎቹ ተናግረዋል። በነሱ ላይ ያለው የፈቃድና የኢኮኖሚ ችግር የሚቀረፍበትን መንገድ ተሰብሳቢዎቹ እንዲያስቡበትም ለተሰብሳቢዎቹ ማሳሰቢያ አቅርበዋል። ከሁሉም በላይ ግን የክርስቲያኖቹ መበታተን አሁንም እያሳሰባቸው በመሆኑ ከቤተክርስቲያን በኩርፊያ መቅረት እንደማይገባ አስተምረው  ከጸለይን ከተማጸንን የማይሆን  ነገር እንደማይኖር መቀበል ደግሞ ክርስቲያናዊ እምነታችን ነው ብለዋል።
  
በእለቱ

፩   የሕግ ክፍል 
፪   የአባላት ጉዳይ ክፍል
፫   የሕዝብ ግንኙነት ክፍል
፬   የመንፈሳዊ ክፍል

ኮሚቴዎች መዋቀራቸውንና የሥራ መመሪያ መንደርደሪያ ለያንዳንዱ ኮሚቴ መሰጠቱን ዘጋቢዎቻችን ጠቅሰውልናል።   በቅርቡም ኮሚቴው የራሱ የሆኑ መጽሔት እንደሚያዘጋጅ የሕዝብ ግንኙነቱ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተናገሩ ሲሆን በስድብ ሳይሆን እውነትን በመዘገብ ደጋፊን ማበርከት እንደሚቻል በግብር እየታየ መሆኑን ጭምር ተናግረዋል። የእለቱ ስብሰባ በጸሎት ተጀምሮ  በጸሎት መገባደዱን ምእመናኑ ጨምረው እንዳወሱን ልንነግራችሁ እንወዳለን።

መረዋ በዚህ አጋጣሚ ይህንን ስብስብ እዚህ እንዲደርስ ለማድረግ ለጣሩ ሁሉ በተገፉትና  በተሰደቡት ምእመና ሥም ምስጋና  እያቀረበ። መሳደብን እንደበትር፤ አሉባልታን እንደ እምነት፤ ትልቅ ሰውን ማዋረድን እንደ ጀግንነት፤ የሚወስዱትን ልቦ ናቸውን ያራራው ዓይናቸውን ይክፈትላቸው እያለ፡ ትዳር ለማፍረስ፤ ግለሰብ ለማዋረድ ፤ የተነሱትን ከመናቅ በስተቀር፡ የነሱን መንገድ መከተል ግን የድክመትም ድክመት እንደሚሆን ያምናል።  አዛውንቶችን በመሳደባቸው  አሸነፍን የሚሉ የፖለቲካ  ድርጅቶች ካሉ እየከሰሩ መሄዳቸውን እንጂ ማሸነፋቸውን እንደማያሳይ ማረጋገጥም ይወዳል ። ሳይሰደቡ ትዳራቸው የፈረሰው የተሳዳቢዎቹ እንጂ የተሰዳቢዎቹ አለመሆኑንም መጥቀስ አስፈላጊ ይመስለናል። ለልጆቻችን ምን እያስተማርን ነው?  ብለን መጠየቅ ያለብን ደግሞ  ሁላችንም ነን። እከሌ  ዘሩ እንደዚህ ነው ብሎ በዘር ግለሰብን መፈረጅ ደግሞ አዋቂነት ከመሰላቸው መቀጠል ይችላሉ። እስከዛሬ የተሰደቡትን ግለሰቦች በማየት ሰዳቢዎቹ እነማን እንደሆኑ ለመገመት በመቻሉ የከተማው ነዋሪ ጥሩ ግንዛቤ  እንያገኘ መሆኑንም መናገር የተገባ ይመስለናል። ይህ ስድብ ደግሞ  ኢትዮጵያዊ ባህላችን አለመሆኑን የሚቀበል ማናቸውም የክርስቲያን አባል ይህንን የተቌቌመውን ኮሚቴ እንዲቀላቀል መረዋ ጥሪውን ያቀርባል።

ከቁልቌል ዛፍ እንጆሪ ይበቅላል፤ ከዶሮ ጅማት ማሲንቆ ይሰራል፤ ማለት ደናክል በረሃ ጤፍ ለማምረት እንደመጣር ያክል ነውና፡ ተሳዳቢዎቹም ይቀየራሉ ብሎ ማለም እንዲሁ ውሃ እየናጡ ቅቤ እንደ መጠበቅ ነው እንላለን።

ለኮሚቴው መልካሙን እየተመኘን የኮሚቴው ልሳን የሆነው መጽሔት ሥራውን ሲጀምር መረዋ የአባላትን የበላይነት በመቀበል የብሎግ እትምቱን እንደሚያበቃ ለአንባብያን በቅድሚያ  ልናሳውቅ እንወዳለን።

እስከዚያው በሰላም ያድርሰን።

  

Sunday, August 1, 2010

እስረኛም መብት አለው። ቁጥር ፴፰

እንዴት ከረማችሁ ምእመናን።
እስካሁን ያሰነበተን አምላክ እንዲያከርመን ስንጸልይ፤ ለመልካም ተነስተናልና  ያሰብነውን ከግቡ እንደሚያደርስልንም ባለመጠራጠር ጭምር ነው። ብዙ የስድብ ውርጅብኝ ሰማን ችግራችን ግን አልተፈታም። ግለሰቦች የግል ሕይወታቸው አንሶላ ውስጥ አደረጉት የተባለው ሳይቀር ለአደባባይ ተነገረ  ችግራችን ግን አልተፈታም። መንፈሳዊ አባቶችን ከክርስቲያን በማይጠበቅ ቃላት ሲዘለፉና ሲወነጀሉ ሰማን ችግራችን ግን አልተፈታም። ቤት ትዳር ያላቸውን ካህን አንዴ  መምሬ  ወረድ ብሎ ደግሞ መነኩሴ  እያሉ ሲዘልፏቸው ሰማን ችግራችን ግን አልተፋታም።  ታዲያ  ስድቡ ለውጥ ካላመጣ መፍትሄ የሚገኘው እንዴት  ነው?  ብሎ  መጠየቅ ያዋቂ ብልሃት ነው እንላለን። አንድ በቅርብ የምናውቀው  ጔደኛችን  ስለሚጻፈው ስድብ ስንወያይ ያለውን እናካፍላችሁ። "በመጀመሪያ የተሰደቡት ግለሰቦቹ ሳይሆኑ ሕብረተሰቡ መሆኑን እንቀበል። የሰዎችን ጥፋትና  ድክመት መጠቆም፡  በሃሳብ ላይ መለያየትና  መከራከር  የተገባ ሆኖ ሳለ ግለሰቦችን ለማስፈራራት ያልተደረገ ፈጥሮ የስም ማጥፋት ዘመቻ ሲጧጧፍ ግን ባንድ ላይ ተነስተን ማውገዝ ሲገባን በዝምታ  መመልከታችን ለችግሩ ተባባሪ ያደርገናል። እስቲ የማውቀውን ላካፍላችሁ"  ያለን ይህ ግለሰብ "የማውቀውን ስላልተናገርኩ እኔንም ጥፋቱ ይመለከተኛል"  በማለት የሚከተለውን አጫወተን።

"በዚህ የስድብ ብሎግ ላይ ተፈራወርቅን እየተሳደቡ ቆይተው የሆሎታ  ምሩቅ  እንደሆነ ከሆሎታም የስንተኛ ኮርስ እንደሆነ  ጭምር  ሁሉ ጠቅሰው ዋሽተው ጽፈዋል። የሚገርመው ዘጋቢዎቹ ይህንን ያሉት አውቀው ሳይሆን የተደጋገመው ውሸት እውነት መስሏቸው ሊሆንም ይችላል። እውነቱ ግን ተፋራወርቅ በ 1965 ዓ ም  እንደ ኢትዮጵ አቆጣጠር ከሐረር መድሃኒዓለም 2ኛ ደረጃ  ት/ቤት ተመልምለው ከገቡት የቀዳማዊ ኃይለስላሴ  የሐረር  ጦር አካዳሚ 19ኛ ኮርስ  አባል መሆኑን ላሳያችሁ ብሎ በ1999 መስከረም ላይ የታተመውን የጦር  አካዳሚውን መጽሃፍ አሳየን። መጽሐፉ ከ1950-1969ዓ ም ያለውን ያካተተ በፎቶግራፍ የተደገፈ ሆኖ  አገኘነው። የሚገርመው በመጽሐፉ ላይ የያንዳንዱን  መኮንን የትምሕርት ደረጃና አሁን  የት እንዳለ  ጭምር  የሚዘግብ ሆኖ  አነበብን። ለናሙና   ያክል ተፈራወርቅ አሰፋ  ሻለቃ እንደነበረና በማኔጅመንት የመጀመሪ ዲግሪውን ከአ አ ዩንቨርሲቲ  ማግኘቱን ብሎም በሶቬት ህብረት የማስተር ዲግሪ በፖለቲካ  ሳይንስ መመረቁን ይናገራል። ይህ እውነት እያለ  ለምን ይዋሻሉ ለሚለው አሁንም መልሱን ለናንተ እንተዋለን። ሻለቃ ተፈራወርቅ ያደረጉት ጥፋት ካለ መናገር መንቀፍ ሲቻል ካልነበሩበት ነበሩ ማለት ግን ወንጀል መሆኑን ማወቅ የተገባ ይመስለናል። ጥፋትን መጠቆምና  ሂስ ማቅረብ ሌላ ስም ማጥፋት ደግሞ  ሌላ።  የየካ ሚካኤል አስተዳዳሪ የነበሩትን አባት አልወደድንዎትም ማለት ሌላ ነገር ሆኖ  እያለ  ያላደረጉትን እያነሱ ያልሆኑትን እየፈጠሩ መሳደብ  ክርስቲያናዊ የሚሆነው የቱ ላይ እንደሆነ ሊገባን ግን አልቻለም ?  በውሸት ተሞልተው በቂም በበቀል ተጠቅልለው "ንስሃ  ግቡ"  የሚሉት ጸሃፊዎች ንስሃ  ምን እንደሆነስ  ያውቃሉን?  ብሎ ቢጠይቅ ጠያቂው እውነት አለው።

ችግራችን የሃይማኖት ሳይሆን የመብት ነው የምንለውም ከዚህ በመንደርደር ነው። እነዚህ በስድብ የተካኑ የብሎግ ጸሃፊዎች ከአስተዳደር ቦርዱ ጋር ያላቸውን ቅርበት ለማወቅ ደግሞ  እሩቅ መሄድ የሚያሻ  አይመስለንም። ባለፈው ተደርጎ  በነበረው ስብሰባ  ለይ ምን አጀንዳ  እንደነበረ ያነበብነው ስብሰባው ከመደረጉ በፊት በዚሁ ብሎግ ላይ እንደነበረ  መጥቀሱ ተገቢ ይመስለናል። ለቦርዱ በጽሑፍ ጥያቄ  ያቀረቡ ግለሰቦች መልሳቸው ሳይነገራቸው መከልከላቸውን የሚሰሙት በዚሁ በብሎግ ላይ ካነበቡ በኋላ  መሆኑን ይናገራሉ። ከቦርዱ ጀርባ የወደፊት እጣችንን  የሚወስኑልን የከተማችን ፈላጭና  ቆራጮች እንዳሉ ደግሞ ከሂደቱ ማየት ይቻላል። የቤተክርስቲያኑ ሊቀመንበር በመሃላ ባለፈው በፍርድ  ቤት ባስገቡት  ቃላቸው ላይ እዚህ ያሉትን መሃበረ ቅዱሳንን "የኮሚኒስት የናዚ የወጣት ሊግ አይነት ናቸው"  ሲሉ የተናገሩትን አውቀውት ነው ለማለት እንቸገራለን።

ስለ መብት በተነሳ  ቁጥር"አባል አይደላችሁምና አባል ሁኑና  እናወራለን " የሚሉት ቡድኖች የማይነግሩን ነገር ቢኖር።

1 አባል ለመሆን ፈቃጁ ቦርዱ መሆኑን "Amended Bylaw Article 2.1"

2 አባልነት ቢፈቀድ እንኴን አንድ ዓመት  ስብሰባ  የመካፈልና  የመምረጥ መብት እንደሌው "Amended Bylaw Article 2.1"

3 በአባላት የተመረጠው  ቦርድ ከአባላት በላይ መብት እንዳለው:: 2/3 አባላት ሳይስማሙበት (ምልአተ  ጉባኤ ሞልቶ በስብሰባ ላይ ከተገኘው   ውስጥ 2/3 ሳይሆን ከጠቅላላ አባላት ማለት ነው) ሕጉን ማሻሻል አይቻልም እያሉ በ2/3 ድምጽ ያልተመረጠው ቦርድ ግን ሕግ መቀየር ይችላል ማለታቸውን

5 አስመራጭ  ኮሚቴውን የሚመመረጠው ከኮሚቴ አባላት መሆኑን ሲናገሩ ኮሚቴውን የሚፈጥረው ግን ቦርዱ መሆኑን "ARTICLE 2.10"

6 ለቦርድ እጩ የሚሆን / የምትሆን ግለሰብ 2 ዓመት በኮሚቴ  አባልነት ያገለገሉ ወይንም 10 ዓመት በአባልነት የቆየ መሆን እንዳለባቸው ሲናገሩ ኮሚቴ  ውስጥ የሚገቡትን መራጮቹ የቦርዱ አባላት በመሆናቸው ለተመራጭነት የሕዝብ ድጋፍ ሳይሆን የቦርድ ፈቃደኝነት እንደሚያስፈልግ "ARTICLE 2.1"

7 ስብሰባ  ተጠርቶ  ሁለት ጊዜ ምልአተ  ጉባኤው ካልሞላ  አሁንም  በመጨረሻ  የተሰበሰበው ሕዝብ በድምጽ ብልጫ ይወስናል ሳይሆን ቦርዱ የተስማማበት ተፈጻሚ ይሆናል እንደሚል "ARTICLE 2.6"

8 ቦርዱ በማናቸውም ጉዳይ የቤተክርስቲያኑ ሃላፊ ነው በማለት ከአስተዳደር ባሻገር የሃይማኖትን ስልጣን  መጠቅለሉን "ARTICLE 1.1,  4.3, 7.3....." 

9 መተዳደሪያ  ደንቡ ላይ ያለው መብት ለሚደግፉት የሚሰራ ለተቃወመ የሚሰረዝ መሆኑን " ARTICLE 7.3, 7.1, 2.9, 9.1"

እነዚህንና የመሳሰሉትን ሸፋፍነው ማለፋቸው ነው። ታዲያ  በርእሱ ላይ እንደጠቀስነው የመብት  ነገር ሲነሳ እኛ መብት ስንል በኩልነት ላይ ያለ  መብት እንጂ   "ሁሉም  ሰው እኩል ነው ጥቂቶች ግን የበለጠ እኩሎች ናቸው" የሚለውን የሰነበተ  THE ANIMAL  FARM መጽሐፍ አይነት ማለታችን   አይደለም።  ስለመብት ካነሳን የታሰረም እስረኛ በእስር ቤቱ የተወሰነ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን የሚዘነጋው የለምና።

ስለመብት እንታገላለን የሚሉ ቡድኖች መብት እንዲደፈር ሲታገሉ ስናይ እናዝናለን። ስለሃይማኖት የሚሰብኩ ደግሞ  የስድብ አለንጋ  ሲያወርዱ ስናይ ደግሞ ምን እርግማን ነው ብለን እንተክዛለን። ባለፈው በነበረ የምእመናን ስብሰባ  ላይ ተነስተው የተናገሩት ግለሰብ "እኔ  መሰደቤ  መልካም ባገራችን እሬሳ  እናከብራለንና የሞተ ወንደሜን ስሙን ማንሳታቸው ግን ተሰማኝ" ሲሉ ከልብ ያላዘነ አልነበረም። "ከቤተክርስቲያኑ ፎቅ ላይ ሕጻናትን ሊወረውሩ ማቀዳቸውን ሰምቻለሁ" የሚሉትን ካመንን ምንም ነገር ማውራት ይቻላል። "ነገ በሬ ምጥ ያዘው እርዱን" ሲሉ ብንሰማ አይገርመንም ማለት ነው። ድሮ  አንድን ተናጋሪ "የወሬ አባትህ ማነው?" የሚሉ ግለሰቦች ዛሬ ለምን ይህንን ይሉ እንደነበር እየገባን እየመጣ ነው።

ታድያ መፍትሄው ምንድነው ለሚለው? መፍትሔው የአማንያንን መብት መጠበቅ ብቻ ነው። እምነትንና አስተዳደርን መለየት ካልተቻለ አሁንም ችግር ይኖራል። የብዙሃኑን መብት መርገጥ ለጊዜው ተችሎ  ይሆናል መረገጥህን ተቀበል ማለት ግን  የሚቻለው ማንም አይኖርም።
በእኛ እምነት የግለሰብን መብት እስካከበርን ድረስ የብዙሃኑን መብት ማስከበራችን ነው ብለን እናምናለን።

የእግዚአብሔር እርዳታ  ይታከልበት

ሰላም ሁኑ