Friday, December 31, 2010

በኢሜል ከደረሰን

ውሸታም ሰው ተፈጥሮው ነው። ተቀብሎ ውሸትን የሚያሟሙቀው ግን አደገኛ ነው።

ወድ አንባብያን በዚህ ጽሁፍ ብዙ ለማለት አልፈልግም። በቅርቡ ሰፋ ያለ በእውነት የተደገፈ  ማስረጃ በዳላስ ኢኦቲሲ ጦማር (DALLASEOTC.BLOG)ላይ በወዳጄ  በአቶ  ተኮላ መኮንን ላይ የተነዛውን በሬ ወለድ ጽሁፍ ወደ መጣበት ይመለስ ዘንድ ሙግቴን አቀርባለሁ። ለዛሬ ግን በዚህ በዳላስ ኢኦቲሲ በሚባል ጦማር ላይ የሚነዛው የውሸት ቧንቧ በተለይ ሰሞኑን በሃዘን ሁሉም የዳላስ ኢትዮጵያዊ ባዘነበት ሰሞን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በጎደለው መንገድ ስለሃዘኑ የጻፉት ሲያሳዝነኝ ይባስ ብለው የውሸት ወሬ ተቀብለው ሲደልቁት ሳይ በዝምታ መታለፍ እነደሌለበት በማመኔ ትንሽ ለመጫር ተገደድኩኝ። ለማንኛውም በቅርቡ በሰፊው እመለስበታለሁ ለዛሬው ለሁላችሁም መልካም አዲስ አመት እያልኩ ከበሬ ወለደ ወሬኞች ያድነን እያልኩ እሰናበታችኋለሁ።


ደም መላሽ ደበበ
ከዳላስ
12/31/2010 4:00 ፒ መ




መከበር ላልፈለጉበተደጋሚ ለማስፈራራት በማሰብ የስድብ ውርጅብኝ በዳላስ ኢኦቲሲ ሲሰነዘርብኝ ቆይቷል። ሁሉንም በንቀት በማለፌ ዛሬ በሬ ወለደ አሉባልታ እየነዙ ይገኛሉ። ለተጻፈው ውሸት በዳስ የሚኖሩ ሳይቀር በብዛት የሕይወት ምስክሮች በአሜሪካ ስለሚገኙ ደንታም አይሰጠኝም። የውሸት ስም ማጥፋትና የአንድ ወር ማስጠን ቀቂያ ግን ሕጋዊ መብቴን መጋፋት በመሆኑ ቤተሰቤንና ሕይወቴን ለመጠበቅ የሚቻለኝን ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ተገድጃለሁ። መረዋ ባይኖር ኖሮ መተንፈሻ ቦታ አናገኝም ነበር።



From: TEKOLA MEKONEN Add to Contacts


To: Yetayal ewnetu





ለመረዋ ምስጋናዬ የላቀ ነው።



ተኮላ መኮንን

t.mekonen@verizon.net

Wednesday, December 29, 2010

በሐዘን የሚቀልድ ደካማ ሰው ብቻ ነው። ቁጥር ፶፬

ውድ የመረዋ አንባብያን ሰሞኑን የደረሰብን ሐዘን መሪር ነበር።  ሁሉም በወጣቱ ልጃችን በማትያስ ከበደ ብርሃኑ ሞት እጅጉን ለማዘኑ በወቅቱ ተሰብስቦ የነበረውን ምእመን ለቅሶ በማየት መገመት ይቻል ነበር። ወጣቶችና ሕጻናት ከመካከላቸው የተለየውን ጨቅላ ለመሰናበት ተሰብስበው የተናገሩትን ሁሉ ስናስታውስ ልጆቻችን ከኛ የተለየ አመለካከት፤ ከእኛ ዘንድ የራቀ ፍቅር እንዳላቸው አየንና በነሱ ተስፋ ተጽናናን። የቤተክርስቲያኑ መሪዎችም ልባቸው በሐዘኑ ተነክቶ የቤተክርስቲያኑን  አዳራሽ መፍቀዳቸውን ስናይ ደግሞ ሚካኤል ዋጋቸውን ይክፈላቸው እንዳልን ሁሉ በሐዘንም ፖለቲካ ሲጠቀሙ ማየታችን ግን አሳዝኖናል። ሊነበቡ የተዘጋጁትን ጽሑፎች እንዳይነበቡ  መከልከል አግባብ አልነበረም። ጽሑፉን ያዘጋጁትን ግለሰቦች ለመቅጣት በማሰብ ሃዘንተኛውን አብሮ መቅጣት በኛ አመለካከት ትክክል አልነበረም። አቶ አበበ ጤፉና አቶ ሙሉአለም ስለ ግለሰቦች ከመፍረዳቸው በፊት እራሳቸውን ቢያስተውሉ ኖሮ   እንደዚያ አይነት ውሳኔ ላይ ባልደረሱም ነበር።  ሰውን በፍቅር እንጂ በጥላቻ ማሸነፍ አይቻልም። ያም ሆነ ይህ ሐዘኑን ተወጣነው። በድጋሜ ዛሬም ለልጃችን ዘለዓለማያዊ እረፍትን ለወላጆቹ ጽናትን ለቤተሰብና ጓደኛ ብርታትን እንለምናለን።

በዚሁ ባለፈው ሳምንት ለብዙ ጊዜ አብረውን የነበሩ እናታችን ወይዘሮ ሰናይት ኃይሌም ከመካከላችን ተለይተውናል። ከጅምሩ የዚህ ቤተክርስቲያን መስራች የነበሩት ወይዘሮ ሰናይት ኃይሌ ለዳላስ ሚካኤል ያበረከቱት አስተዋጽኦ ቀላል አልነበረም። ልጆቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ጭምር ለሚካኤል እድገት አስተዋጽኦ ያደረጉ ግለሰቦች ሥም ሲጠራ የመጀመሪያውን ስፍራ እንደሚይዙ የማይስማማ  ግለሰብ ቢኖር የቤተክርስቲያናችንን ታሪክ የማያውቅ ወደ ከተማችን በቅርቡ ጎራ ያለ ብቻ ይሆናል።  ለወይዘሮ ሰናይት መንግስተ ሰማያትን ለልጆቻቸውና ቤተሰባቸው  መጽናናትን መረዋ  እየተመኘ፡ የሐዘናቸው ተካፋይ እንደሆነም  ይገልጻል።

ይህንን ካልን ዘንዳ፡

በዛሬው እለት የምናስነብባችሁ የዳላስ ምእመን በመላ በሐዘን ላይ እያለን የቦርድ ደጋፊዎች ነን የሚለው ጦማር (BLOGS)በገጹ ላይ የለጠፈውን ጽሑፍ ነው። ጽሑፉን እንዳለ ገልብጠን ለአንባብያን አቅርበነዋል። ከዚህ በታች ያለውን አንብቡና ፍቀር እምነት እያሉ የሚሰብኩን አስመሳዮች ለሐዘን ደንታ የሌላቸው ፈሪሃ እግዚአብሔር የራቃቸው ለመሆናቸው ምስክር የሆነውን ብእራቸውን እዩላቸው።እኛ ባባላቸው ካዘንን በ ድርጊታቸው ከተጸጸትንላቸው ቆየን። የጻፉት ጽሑፍ ከዚህ በታች አቅርበንላችኋል መልካም ንባብ። 
[Post a Comment On: Dallaseotc"የተጀመረው መሻሻል ከግቡ እንዲደርስ"




2 Comments - Show Original Post

በጎረቤታችን ላይ የተንኮል ተግባር ከመፈጸማችን በፊት በአምላክ ፊት ምን እንደሚጠብቀን አስቀድመን ብናውቅ ሁላችንም የመጀመሪያውን ድንጋይ ለመወርወር ባልቃጣን ነበር። በዚህ በያዝነው ሳምንት ውስጥ ፈጣሪያችን አምላካችን ለ ዳላስ አካባቢ የክርስቶስ አማኞችና የቅዱስ ሚካኤል ምእመን ብዙ ተአምር አሳይቶናል። እንድንጠነቀቅም ፊታችንንም ወደ ፈጣሪያችን እንድንመልስ ሊያደርገን ሁለት ተአምር አሳይቶናል። አንደኛው የቤተክርስቲያናችን አባል የሆነው ጸሃፊያችን የልቡን አይቶ ሃጢአት ውስጥ እንዳይገባና እንዳይረክስ መልአኩን በ ፖሊስ መልክ ልኮ ከ መጥፎ ተግባር እንዲድን አድርጎታል።




ባኳያውም የዚህን ግለሰብ ኅጢአት ከፖሊስ ሰነድ ውስጥ አውጥቶ በየታክሲያችን ላይ ሲበትንና ያገሩን ልጅ ስም ሲያጠፋ የነበረው ( ስሙን በደረሰበት አደጋ ምክንያት ለመጥቀስ በማንፈልገው ግለሰብ ) ላይ በደረሰው የአባት ሃጢአት ለልጅ በተላለፈ አደጋ ልጁን ያጣው ሰው የቅዱስ ሚካኤልን ደጀ ሰላም መጥናኛ እንዲሆን ያውም በትምህርት ቀን ያስፈቀደለት ማን ይመስላችኋል!


መድረኩን ማስፈቀድ ብቻ ሳይሆን ቀሳውስቱና ዲያቆናት እንዲተባበሩ ለማድረግ ብዙ ጥረት ያደረገው ሰው ነው። አሱም ፤በ እኔ ላይ የራሱን ጉድ ደብቆ ልጆቹን በትኖ ብህግ ያገባት ሚስቱን የልጆቹን እናት


ጥሎ ወደ ሴተኛ አዳሪ ቤት የገባ ሰው የኔን ሃጢአት እያጋነነ ለጠላት ስለሰጠብኝ ብሎ አልተቀየመውም። ይሄን ያልነው እኛ ጉዱን የምናውቅ ነን። ይልቅስ በማያውቀው ሓጢአት ዉስጥ ገብቶ ልጁን ማጣቱ አሳዝኖት እንደማንኛችንም ሲያለቅስ አምሽቷል። ታዲያ እኛ እን ማን ሆነን ነው የቅዱስ ሚካኤልን ሥራ ነገ በኛ ላይ የሚደርሰውን አዉቀን የሰው ስም ለማጥፋትና በሃሰት ሰው ለመክሰስ እምንመኘው።


ለዚህ ነው ነገ የሚደርስብንን ብናውቅ ዛሬ እማጥ ውስጥ አንገባም ነበር ያልኩት። በሰው ላይ ተንኮል ለመስራት አንሯሯጥ ሰው ባያውቅብን እግዚአቤሔር ያውቀዋልና፤ ከሱ የሚሸሸግ ነገር እንደሌለ እንወቅ።


አሜን;






December 18, 2010 1:52 PM]

ይህ የኛ ሳይሆን የአስተያየት ሰጭዎች ነው ሊሏችሁ ይነሱ ይሆናል። እውነቱ ግን እነሱ አንብበው ያጸደቁት ብቻ እንደሚወጣ እራሳቸው የሚክዱ ካለመሆኑም በላይ በጦማራቸው BLOGS በአስተያየት መስጫ አምዳቸው በግልጽ ሃላፊነት እንደሚወስዱበት አንብበው እንደሚለጥፉት የተጻፈ ነው። 
እነዚህ ከሆኑ የእምነት ሰዎች በእውነት ብዙ የሚያነጋግረን ጉዳይ አለን። እነዚህ ከሆኑ የመሪዎቻችን ደጋፊዎች ወንድሞቼ ቤታችንን ለማፍረስ ትልቅ ትግል እየተካሄደ ነው። እነዚህ ከሆኑ የቤተክርስቲያናችን አንጋፋዎች ቤተክርስቲያናችን ሽማግሌ የለበትም የሚያሰኝ ነው። ይህ ከሆነ ሐዘንተኛን ማጽናናት ወንድሞቼ ለእናንተው ፍርዱን እንተዋለን። በባህላችን ከምንም በላይ ሃዘንን እናከብራለን። ያንን የማይቀበል ስለሐዘን ደንታ  የሌለው ብቻ  ነው። በመሳደብ ለወጥ ሲመጣ አላየንም። በማስፈራራት ደግሞ ፍቅር አይገነባም።   

የሳምንት ሰው ይበለን።

Saturday, December 18, 2010

ለጭቅጭቅም ለሐዘንም ጊዜ መምረጥ የተገባ ነው። ፶፫

ውድ አንባብያን

ሰሞኑን ያጋጠመን ሐዘን በጣም የከፋ ነው። ሐዘኑን የከፋ  የሚያደርገው ቆመን ያዋለድነውን ማቲው ሃይሌን እድገቱን ሳይጨርስ ቆመን ለመቅበር በመነሳታችን ነው።  ማቲውን ስናስብ ልጃችን ነውና  ልጆቻችን ይታዩናል። ማቲውን ስናስብ የዓለማዊ ሽኩቻችን የእድሜ ገደብ እንደሌለን አድርገን የምናስበውን  እንደገና እንድንመረምር ይገፋናል። ስለሆነም መረዋ የዚህን ከመካከላችን የተወለደውን በጨቅላ  እድሜ የተቀጨውን ወጣት ዜና እረፍት ምክንያት በማድረግ አስከሬኑ ግብአተ  መሬት ሳያርፍ ምንም አይነት እትምት ላለማውጣት ወስኗል።

ለማቲው ደስታዊ ዘላለማዊ እረፍትን
ለቤተሰቡ መጽናናትን እንመኛለን

በዚህ አጋጣሚ በነገው እለት በቅዱስ ሚካኤል አስተባባሪ ኮሚቴ ተጠርቶ የነበረው የምእመናን  ስብሰባም በሐዘኑ ምክንያት ለሚመጣው ወር አጋማሽ መተላለፉን ከኮሚቴው የወጣው መግለጫ አስታውቋል። በበለጠ ለመረዳት የምትፈልጉ የኮሚቴውን ጦማር በመጎብኘት መረዳት ትችላላችሁ።


የሳምንት ሰው ይበለን

Monday, December 13, 2010

የተደናቀፈ ሰው አጠገቡ ያለውን ይዞ ይወድቃል ቁጥር ፶፪

ቴክሳሶች አንድ መኪና ላይ የሚለጠፍ መፈክር አላቸው። IF YOU GO TO HELL DON'T BLAME IT ON JESUS  "ሲኦል ብትገባ በክርስቶስ አታመካኝ" የሚል ነው። ወደ ገሃነም እንዳትገባ ክርስቶስ ላንተና ለኔ ሐጥያት ደሙን እስከማፍሰስ ደርሷልና  ማለታቸውም ነው። ታዲያ

ለሠራንው ምስጋና እንደምንቀበል ሁሉ  ለጥፋታችንም ሃላፊነት መውሰድ ካልቻልን ደካሞች ነን።
ስለሌላ ሰው ድክመት ማውራት ቀላል ነው ስለራስ ድክመት መናገር ግን ቆራጥነትን ይጠይቃል።
ሰው ያልዘራውን አያጭድም።
አለማወቅን መቀበል አዋቂነት ነው።
በንስሐ የማያምንን ሰው ቅስፈት አለ  ብሎ  ለማስተማር መሞከር የዋህነት ነው።

ውድ የመረዋ አንባብያን። የቤተክርስቲያናችን ችግር እየባሰ እንጂ እየተሻለው እንዳልመጣ ምስክሮቹ እናንተው ናችሁና መናገር አስፈላጊ አይመስለንም። ፍቅራችን የትሄደ? ብሎ ለጠየቀ አንድ ወንድም "አሁንስ ድሮም እንደነበር እየተጠራጠርኩ ነው።" ያሉት እናት ተስፋ ቆርጠው ለመናገራቸው ጠቋሚ አላስፈለገንም። እኚህ በየሳምንቱ በማዶው ጦማር ስማቸው እየተጠቀሰ የሚሰደቡትን አዛውንት ለመሆኑ ጥንካሬና ትእግስት ከየት አመጡ? ተብለው ሲጠየቁ ጠዋት ከምደግማት ውዳሴ  ማርያም  ማታ ከማነበው መጽሐፍ ቅዱስ ነዋ ልጄ ማለታቸውን የነገረን በቅርብ የሚያውቃቸው ጓደኛቸው ነው። ገንዘባቸውን ባፈሰሱ፤ ቀሳውስቶችን በረዱ፤ አበስ ገበርኩ ብለው ሥጋወደሙ በተቀበሉ የዚህ ቤተክርስቲያን አመራር ደጋፊዎች ነን ባዬች በየጦማሩ ሲያብጠለጥሏቸው፤ ከትዳራቸው ሊያፋቱ፡ ቤተሰባቸውን ሊበትኑ ሲዘምቱ "ፍቅር ብናሳያቸው እናሸንፋቸዋለን" ብለው ተሰዳቢው መልስ ሲሰጡ መስማት ላዳማጭ ውሸት ቢመስል ምን ይገርማል። ነገሩ ግን ባይገርማችሁ እውነት ነው።

የሰደቧቸው ሰዎች የሰደቡት ሁላችንንም ነው። የተሳደቡት የከተማውን አንጋፋዎች ነው። የተሳደቡት እራሳቸውን ነው። "ጎጃሜ ነኝ የሚለው ዘሩ ትግሬ የሆነ" ሲሉ የተባለው ግለሰብ የትግራይ ተወላጅ አለመሆኑን ስላወቅን ብቻ  ሳይሆን ቢሆንስ ከትግራይ መወለድ ሃጥያት ነውን? ብሎ  የሚጠይቃቸው ሰው የጠፋው ነገ  እኔን ደግሞ  ብናገር ያልተወልድኩበትን ሰፈር ይለጥፉብኛል ብሎ  በመስጋት ይመስለናል። ከተወሰነ ብሔር መወለድ ክብር የሚመስላቸው አሁንም ከዘር አረንቋ ውስጥ የተዋጡ ጊዜአቸው ያለፈባቸው ትምክህተኞች ብቻ  ናቸው።

ፖለቲከኛ ለመሆን እኮ እውቀትን ይጠይቃል።
ለዘረኝነት ግን መሃይምነት መፈልፈያ ቅርጫቱ ነው።

በዛሬው ምሽት የምስራች ይዘንላችሁ አልቀረብንም። የደሰታ መረዋ ልንመታ አልተነሳንም። የሃዘን ማቅም አላጠለቅንም። እንዳንናገረው እየፈራን እንዳንተወው እያናደደን ይዘንው ቀረብን እንጂ። ነገሩ እንዲህ ነው።

የሚካኤል ደብር አስተዳዳሪ ቦርድ ጸሐፊ የሆኑት አቶ  አበበ (ጤፉ) ባለፈው ዓርብ እለት ከፍርድ ቤት ውሎ ምሽት መሆኑ ነው: የመንገድ ሴትኛ አዳሪ ሲያነሱ ተገኝተው ታስረው እንደነበር የዳላስ ፖሊስ በድህረ ገጹ ላይ ከነፎቶግራፋቸው እንዳወጣ ተደውሎ  ሲነገረን ያልነው ነገር ቢኖር "ሚካኤል እውነትም ተቆጥቷል" የሚል ነበር። በተለይም ድርጊቱ ተፈጸመ  የተባለው በቀጠሮው ቀን መሆኑ ሁላችንንም ሳያስገርም አልቀረም። አቶ አበበ ዓርብ ታስረው እሑድ ከቤተክርስቲያን መጥተው የምእመናንን  ዓይን እያዩ  ማስታወቂያ መናገራቸው ቢገርመንም የሳምንቱ እሑድ ሳይደርስ የተከበረ  ቤተክርስቲያናችንን እንደተከበረ  እንዲኖር ባስቸኳይ ከሃላፊነታቸው እንዲለቁ መረዋ  ምክሩን ይለግሳል። የተደናቀፈ ሰው አጠገቡ ያለውን ይዞ ይወድቃልና፡ አብረው ያሉትም የቦርድ አባላት ሰላሙን ለመፍጠር በፈቃዳቸው ቢሰናበቱ ለሚመጣው ችግር መፍትሄ ይሆናል ብለን እናምናለን።

መረዋ ለአቶ  አበበ ጽናቱን እንዲሰጣቸው ይጸልያል።

ከፈተና ያድናችሁ።

Friday, December 10, 2010

የፍርድ ቤት ውሎ ቁጥር ፶፩

እንደምን ዋላችሁ

ከትላንትና ወደ ዛሬ  በዳኛው ጥያቄ  የተዛወረው የፍርድ ቤት ቀጠሮ በዛሬው  እለት ከሳሾችና ደጋፊዎቻቸው፤ ሰዎስት የቦርዱ "ሹማምንት" በተገኙበት ሲሰማ  ውሏል። በወቅቱ "ከሳሾቹ አባላት ባለመሆናቸው ብሎም ከዚህ በፊት በዚህ ፍርድ ቤት በከሳሽነት ቀርበው የተበየነባቸው በመሆኑ ክሱ ተደጋጋሚ ነውና ዛሬውኑ ተሰርዞ በነጻ አሰናብተን" ብለው ጉዳዩን ወደ ዳኛው ያመጡት የቦርዱ ጠበቆች ሲከራከሩ ስናይ  ባለፈው  እንደ ሰማነው እንጂ የተቀየረ  ነገር እንዳልነበረበት ለመታዘብ ችለናል። ከዚህ በፊት የነበረውን ክስ እንደማያውቁ የተናገሩት የከሳሾች ጠበቃ ዳኛው ከዚህ በፊት የወሰኑትና ይህ እሳቸው የመሰረቱት ክስ እንደማይመሳሰል ለዳኛው አስረድተዋል። በመሆኑም ዳኛው ባለፈው የወሰኑት ቦርዱ መተዳደሪያ ደንቡን መቀየር ይችላል አይችልም በሚል ላይ መሆኑን የጠቆሙት የከሳሾች ጠበቃ አንድም ቦታ መተዳደሪያ  ደንቡ ትክክል ነው ብለው ዳኛው እንዳልወሰኑ በተለይም የቦርዱ ምርጫ ሕገወጥ መሆኑን አስመልክቶ ምንም የተናገሩት እንደሌለ ጠቁመው የሳቸው ክርክር መሰረቱ የቦርድ አባላት ከሕግ ውጭ የተመረጡ በመሆኑ ይህንን በማስረጃ  አስመርኩዤ ለመከራከር የሚከለክለኝ ምንም ነገር ሊኖር አይችልም ብለዋል። ዳኛው በዚህ ጉዳይ ላይ ውሳኔ መስጠቴን የሚያሳይ መረጃ አላችሁ ወይ? ብለው የተከሳሾችን ጠበቆች ቢጠይቁም የቦርዱ ጠበቆች ሊያቀርቡ የቻሉት ባለፈው ክስ ላይ የድሮው ጠበቃ የተናገሩት ንግግር ብቻ ነበር። የቦርዱ ጠበቆች ያቀረቡትን ያለፈ የጠበቃ የመከራከሪያ ነጥብ ንግግር ዳኛው አንብበው ይህንን ሳይሆን እኔ የወሰንኩበትን ነው የምለው በማለት በድጋሜ ጠይቀው የተከሳሾች ጠበቆች ሊያቀርቡ አልቻሉም።

አባላት አይደሉም ለሚለው የከሳሽ ጠበቃ የቦርዱ አባላት ባወጡት የመተዳደሪያው ደንብ መሰረት የከሰሰ አባል መሆን አይችልም የሚል አንቀጽ እንዳለበት ሲናገሩ፤ ዳኛው እውነትክን ነው እሱን ነገር  እኔም አስታውሳለሁ በማለት ሲስቁ ተመልክተናል።

በተጨማሪም በሚመጣው 12/20/10 በቦርድ አባላት የይግባኝ ጥያቄ መሰረት በዚሁ ፍርድ ቤት ተቀጥሮ የነበረው ቀነ ቀጠሮ አስመልክቶ ወደ እረፍት በዚያን ወቅት እንደሚሄዱ ጠቅሰው እንዲቀየርላቸው የከሳሾች ጠበቃ የጠየቁትን ዳኛው በመቀበል ወደሚመጣው ወር ማለትም 1/20/11 ሲቀይሩት በ1/10/11 የነበረውም ቀጠሮ  እንዲሁ እንዲራዘም ዳኛው ተስማምተዋል። ይህም የሆነው የቦርድ አባላት የተጠየቁትን ጥያቄዎች መመለስ ይኖርባቸዋል ብለው ዳኛው እረዳት ዳኛቸው የበየኑትን ብይን ቢያጸኑት ካጸኑት በኋላ ቢያንስ 30ቀን እንደሚያስፈልጋቸው የከሳሾቹ ጠበቃ በመጠየቃቸው ነበር።  

በወቅቱ ቦርዱን በመወከል ዶክተር ግርማ አቶ  ዮሴፍ ከናባለቤታቸው አቶ አበበ ሲገኙ በታዛቢነት ደግሞ የአቶ አበራ ፊጣ ባለቤትና ወይዘሮ አባይነሽ አብረዋቸው እንደነበሩ አስተውለናል። ከከሳሾቹ ወገን ከሳሾቹ በሙሉ የተገኙ ሲሆን ደጋፊዎቻቸው ባንድ በኩል ተቀምጠው አስተውለናል። ከቦርድ ባለፈው ጊዜአቸውን ጨርሰው የወረዱ ግለሰብ ሳይቀር ሁኔታውን ለማዳመጥ መጥተው እንደነበርም ልንነግራችሁ  እንወዳለን።

በመጨረሻም የተከበሩት ዳኛ ለሁሉም መልካም ገና በመመኘት ውሳኔአቸውን  በሚመጣው ሳምንት እንደሚያስታውቁ ተናግረው የችሎቱ ፍጻሜ  ሆኗል። በስፍራው የተገኙት የመብት ትግሉ ደጋፊዎች ዳኛው ምንም አይነት ውሳኔ ይስጡ ትግሉ እንደማይቆም ቃል ሲገባቡ ለመመልከትም እድል ገጥሞናል።

መረዋ የፍርድ ቤቱ ብይን እንደደረሰው ብይኑን ለአንባብያን እንደሚያቀርብ ካሁኑ ቃል እየገባ በሚመጣው 12/19/10 በድሪምስ አዳራሽ በ1:00 PM ሁላችሁም እንድትገኙ ጥሪውን እንድናሰማ በመጠየቃችን ሁላችሁም ከቅዳሴ መልስ ወደዚያ እንድታመሩ ልናሳስባችሁ እንወዳለን።

እውነት ምን ጊዜም ያሸንፋል

ቸር ወሬ  ያሰማን።

Monday, December 6, 2010

ዘግይቶ የደረሰን

በሚመጣው ሐሙስ DECEMBER 9, 2010 ተቀጥሮ  የነበረው የፍርድ ቤታችን ቀጠሮ በዳኛው ጥያቄ መሰረት በማግስቱ ለ 12/10/2010 በ 9:00 ሰዓት መዛወሩን ዛሬ  ቀትር ላይ ለማወቅ ችለናል። ሁኔታው ከቁጥጥር ውጭ በመሆኑ ፈቃድ ጠይቃችሁ ሐሙስ እለት ፍርድ ቤት ለመገኘት ተዘጋጅታችሁ የነበራችሁ በሙሉ በተፈጠረው የቀጠሮ መጋጨት ከልብ እንደምታዝኑ ይገባናል። አሁንም የቻላችሁ ዓርብ እለት በተባለው ሰዓት በፍርድ ቤት   በመገኘት ለማዳመጥ ብትሞክሩ ምሥጋናችን የላቀ  ነው።

"ሰው ያስባል እግዚአብሔር ይፈጽማል"


Sunday, December 5, 2010

እምነት ያልገዛውን ቡድን ሕግ ያስተካክለዋል ቁጥር ፶

ቤተክርስቲያን እንዴት ይከሰሳል? የሚል ጥያቄ ለሁለት ዓመት ሲጠየቅ መቆየቱ የሚዘነጋ አይደለም።በተለያየ ወቅት ይህንን ጥያቄ አስመልክቶ ባጥጋቢ መልስ የተሰጠበት በመሆኑ ዛሬ በዚያ ላይ ጊዜ ማጥፋት አንፈልግም። እንዳዲስ ተነስተው "ቤተክርስቲያን እናት ነችና እናት እንዴት ትከሰሳለች?" እያሉ ለሚጠይቁ ግን ያገሩን ሕግ ካለማወቅ የመጣ ጥያቄ በመሆኑ እናት መከሰስ አይደለም የእናትነት ግዳጇን ካልተወጣች የእናትነት መብቷ ተገፎ ልጆቿን እንደምትነጠቅ መጠቆም እንወዳለን።ቤተክርስቲያንን እናስተዳድራለን ብለው በደል የሚፈጽሙትን ደግሞ ከመክሰስ ሌላ አማራጭ አይኖርም። አማራጭ ቢኖር በጉልበት መፋለም ይሆናል። ያንን ደግሞ እኛ አጥብቀን እንቃወማለን። በተራችን ለጠያቂዎቹ የምንጠይቃቸው ጥያቄ ግን  አለን። እምነት የማይገዛውን የአመራር ቡድን፤  ሽማግሌ የማያከብረውን የአመራር ቡድን ፤ አዛውንቶችን ለማናገር እንኳን ፈቃደኛ የማይሆንን የቦርድ ተመራጮች፤ የምእመናንን ፊርማ  ያዘለ የስብሰባ  ጥሪ አሽቀንጥሮ  የሚጥልን አንባ ገነን፤ ሕገ ወጥ አሰራሩን ማስቆም የሚቻለው እንዴት ነው ብለው ያስባሉ?

አባትና እናት እየበተኑ፡፡ ወላጆችን ከቤተክርስቲያን እያባረሩ። ልጆቹን እያስተማርን ነው ብለው ሲናገሩ አይቀፋቸውምን?የልጆች ነገር አይሆንልኝም የሚሉት አዛውንትስ የወላጆችን  መበተን  በጸጋ  መቀበላቸው ለምን ይሆን? የሚፈሩት ነገርስ ምንድነው? ይህ ባደባባይ የሚነገር ጥያቄ  ሆኖ እየሰማነው ነው።

ባለፈው ሳምንት ካህኑ "ልጆቼንና ባለቤቴን ሸጠህ ትምህርት ቤት አሰራ"  ብለውኛል ተብሎ ከመቅደስ ሲነገር ተገርመን ነበር። ቤተክርስቲያናችን የሰውን ልጅ መሸጥና መለወጥ የማትደግፍ መሆኗን አለማወቅም አስመስሏል።ነገሩ ለአባባል ተብሏል ሊባል ይችል ይሆናል። ነገር ግን የሚነገሩ ቀልዶች የሚያመጡት መዘዝ እንዳላቸው ማሳሰብ ፈልገን ነው። ያንን ማየት መረዳት ደግሞ የማመዛዘን እውቀትን ይጠይቃል።

ባለፈው እንደነገርናችሁ በአቶ ሰይፉ ይገዙ የሚመራ  የሽማግሌዎች ቡድን የአማራጭ አፈላላጊ ኮሚቴንና የቦርዱ ደጋፊዎች ነን የሚሉ ግለሰቦችን ማነጋገራቸው የሚታወስ ነው። የሽማግሌዎቹ ቡድን ይህንን ካደረገ  በኋላ  ከቦርዱ ጋር ቀጠሮ ይዘው በብዙ ውጣ ውረድ በቀጠሮው ቀን ሲሄዱ ለማነጋገር የጠበቃቸው ቦርዱ ብቻ  ሳይሆን የቦርዱ አጃቢዎች ጭምር ነበሩ። ሽማግሌዎቹ እኛ ልናነጋግር የመጣነው ቦርዱን ነውና አጃቢዎቹን አስወጡልን አላሉም። አብረው መወያየታቸውን ቀጠሉ እንጂ። የቦርዱም አባላት ከአጃቢዎቻቸው ውጭ ለመነጋገር ፈቃደኞች  አልነበሩም።ታዲያ ሽማግሌዎቹ ለመናገር ለምን ፈሩ?  ለሚለው አሁንም መልስ ያላገኘ በግልጽ መቅረብ ያለበት ጥያቄ  ይመስለናል። አቶ  ሰይፉን የተሳደቡት የቦርድ ተመራጭ ባለቤት በአቶ ሰይፉ አንደበት ሲወደሱ የሰማ ግለሰብ ጆሮውን አላምን ብሎ እጎኑ ያነበረውን ግለሰብ ምን እየተናገሩ ነው? ብሎ  እንደጠየቀ ሰምተን ተገርመን ነበር።

ለመሆኑ የቦርዱ አጃቢዎች እነማን ነበሩ

የኢንጅነሩ ተጠሪ  አቶ  አበበ
የቅንጅቱ            አቶ  ደጀኔ
የኢሕአፓው       አቶ  ከተማ
ቶውትራኩ           አቶ መሰለ እንደሚገኙበት ለማረጋገጥ ችለናል።

ሽማግሌዎችን ወክለው የተሰበሰቡት ደግሞ

አቶ  ሰይፉ ይገዙ
አቶ  በትሩ ወልደ አማኑኤል
አቶ  ጌታቸው ትርፌ  እንደ ነበሩም አረጋግጠን ነበር።

ስብሰባው እንደተጀመረ "የምን ብጥብጥ ነው ቤተክርስቲያናችን ሰላም ሰፍኗል" ያሉት የቦርድ ተመራጭ የግንዛቤ እንጂ የአካል እይታ ችግር እንደሌለባቸው ብናውቅም አባባላቸው አንድ ነገር አስታወሰን።

ለጥየቃ  ኢትዮጵያ ሄዶ የመጣ ግለሰብ ዘመዶቼ ደህና ናቸው ቢሆንም እናቴ አርፋለች። አባቴ እኔ እዛ ሄጄ በሚስቱ ሞት ደንግጦ ወደቀና ሞተ። እህቴ በቤተሰብ ሐዘን ተጎድታ አርባቸውን ሳታወጣ እንኳን አለፈች። የቀረ  ዘመድ የለኝም ያለውን ማለታችን ነው።

በስካር መንፈስ በየመጠጥ ቤቱ እደባደባለሁ እገላለሁ እያሉ የሚጋበዙት የቅንጅቱ  አቶ አበበ ዛሬ የትጥቅ ትግል ያሉበትን ያልያዙትን ጠመንጃቸውን  ጥለው መስቀል ይዘው ማየታችን ቢገርመንም ይህ ደግሞ ለመልካም ሆኖላቸው ከስካር ቢያድናቸው መልካም በሆነ ነበር። እንደ ቅንጅቱ ማሕተም የቤተክርስቲያኑን ማሕተም ለንግድ ማዋል ይቻላል ብለው በማሰብ ገብተው ከሆነ እንደማይሳካላቸው ካሁኑ ሊነገራቸው ይገባል።ለማንኛውም በዛሬው እለት በመለከት ጦማር ላይ የወጣው የሽማግሌዎችና የአማራጭ አፈላላጊ ኮሚቴ የመጨረሻ ስብሰባ ያረጋገጠልን ነገር ቢኖር ተመራጮቹ ሰላምን እንደማይፈልጉ ቀደም ብለን የተናገርነውን ማረጋገጡ ብቻ ነው። ሽማግሌዎቹ ካሁን በኋላ ያላቸው ምርጫ ቢኖር ብዙሃን ምእመንን ተቀላቅለው በሕግ መፋለሙን መቀጠል ብቻ ይሆናል። ካልሆነ ዝምታን እንመርጣለን ማለት ሳይመለስ ተንጠልጥሎ ያለውን ጥያቄ ይኸውም የሚያስፈራቸው ምንድነው? የሚለውን የሚቀሰቅስ ይሆናል። ዛሬ ያለው ምርጫ አንድ ነው። የተደፈረውን የምእመናን መብት በሕግ ማስከበር ብቻ ነው። እራሳቸው አውጥተነዋል የሚሉትን ሕግ እንኳን የማያከብሩ የቦርድ ተመራጮች ከዛሬ  ነገ ልባቸው ይራራል ብሎ የሚጠብቅ ካለ፡ የዝሆን ጆሮ አሁን ካሁን ይወድቅ ይሆናል ብሎ  እንደሚከተለው ጅብ አይነት መሆን ይመስለናል።

አቶ  አበበ ጤፉ
አቶ  አበራ ፊጣ
አቶ መሰለና
የቦርዱ ዶክተር ዘማሪ ሆነው መመረቃቸውን ስናይ መመረቅ የማይሰለቻቸው ዶክተር አላልንም ዳላስ በመሪነትና  በዘማሪነት የሚያቀርበው እነዚህን ብቻ ከሆነ  እውነትም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለነው አልን እንጂ።

ይህንን ቤተክርስቲያን ወደነበረበት ለመመለስ ብዙ የበኩላችንን ጥረናል። ታግሰናል። ሲሰድቡን አልተሳደብንም። ሲያስፈራሩን ፍርድ ቤት አልሄድንም። ሕይወታችን አደጋ ላይ እንደሆነ ሲነገረን ፈርተን አላፈገፈግንም። አሁንም የተረገጠ መብታችንን ሳናስከብር ወደኋላ አንልም። ለሽማግሌዎች ልንናገር የምንወደው ስለህጻናት ብዙ ተብሏልና የእኛም ልጆች ሕጻናት መሆናቸውን ነው። የእኛም ልጆች የኦርቶዶክስ ልጆች መሆናቸውን ነው። ወላጆችን አባሮ ልጆቹን እንፈልጋለን ማለት ደግሞ ሕዝብን ገድሎ  አገርን ማስቀረት አይነት መሆኑን እንዲገነዘቡትም እንወዳለን። ከስጋው ጦመኛ የሆነ  ሰው ከመረቁ አይከጅልምና።

በልጆች ስም መነገድ መቆም ይኖርበታል። የሁሉም ልጅ እኩል ነው ብለን እንቀበል።
አቋም ከሌለው ወዳጅ ይልቅ አቋሙ የሚታወቅ ጠላት ይከበራል።

በ DECEMBER 9 በፍርድ ቤት

በ DECEMBER  19 በተጠራው ስብሰባ ላይ ለመገኘት ተዘጋጁ።

በቸር ይግጠመን።