Wednesday, February 9, 2011

ዘግይቶ የደረሰን

እንዴት ሰነበታችሁ ውድ አንባብያን

ባለፈው እትምታችን እንደነገርናችሁ ተከሳሽ የሆኑት የቤተክርስቲያኑ የቦርድ ባለስልጣናት ቀደም ባለው ዳኛ ተወስኖ የነበረውን

በመቅደስ ውስጥ ፖሊስ አታስገቡ
አማንያንን አታባሩ
መዛግብቶችንና የኮሚፒውተር መረጃዎችን እንዳታጠፉ ብሎ የወሰነባቸውን በመቃወም ይግባኝ  ማለታቸው የሚታወስ ነው። በመሆኑም በ2 / 7/ 2011 ያስቻለው የይግባኝ  ሰሚ ፍርድ ቤት በከሳሽና  በተከሳሾች ጠበቆች የቀረበውን የቃል ክርክር አዳምጠዋል። በወቅቱ የተሰየሙት 3 ዳኞችም ለሁለቱም ጠበቆች  እንዲብራራላቸው የፈለጉትን ጥያቄዎችም ጠይቀው መልሱን  አዳምጣዋል።

ከሳሾችን አናውቃቸውም ያሉት የተከሳሾች ጠበቃ ከሳሾች ማክዶናልድ  ምግብ ቤት ሃምበርገር ተመላልሰው በመበላታቸው የማክዶናል የቦርድ አሰራር አላማረንምና የመቀየር መብት አለን እንደሚል ግለሰብ ናቸው ብለዋል። ስለሆነም እኛም ያልመሰለንን  የማስዋጣት የማባረር መብታችን መጠበቅ አለበት ምክንያቱም ቤተክርስቲያን በመሆናችን  መንግስት ጣልቃ  ሊገባብን አይችልም መንግስት መግባት የሚችለው የንብረት ይገባኛል ጥያቄ ይዘው ቢቀርቡ ነበር  ማለታቸውን ለመረዳት ችለናል።
የከሳሾች ጠበቃ በበኩላቸው እነዚህ ተመራጮች ያላግባብ የተመረጡ ከመሆናቸውም በላይ ጥያቄ ተጠየቅን ብለው ሴትና ሕጻናት በተሰበሰቡበት ወገን ፖሊስ እያስገቡ ያሳሰሩ ብሎም መብታቸውን በመጠቀም አባላትን ለማባረር የተነሱ መሆ ናቸውን አውስተው ጉዳዩ የእምነት ሳይሆን የመብት መገፈፍ መሆኑን አስረድተዋል። በ2/10/2011 ዳኛ ስሚዝ በይግባኝ ሰሚነት የሚያዩት ለውሳኔ  የቀረበ  መዝገብ እንዲያሳዩ  በበታች ዳኛ  የተወሰነውን አሻፈረን በማለት አሁንም የቦርዶቹ ጠበቃ ያቀረበው ስለለ የእሱንም ውጤት የይግባኝ  ሰሚው ፍርድ ቤት መጠበቅ ይኖ ርበታል ብለዋል።
ፍርድ ቤቱ የቀኑን የጠበቆች ገላጻ አዳምጦ የእለቱ ሸንጎ ፍጻሜ  ሆኖ ተበትኗል።




ዘግይቶ  የደረሰን ዜና በነገው እለት 2/10/2011 ተቀጥሮ  የነበረው ይህ ቀጠሮ በከሳሾች ጠበቃና በዳኛው የፕሮግራም መጋጨት መተላለፉን ለመረዳት ችለናል።  የቀጠሮውን ቀን እንደደረሰን ለአንባብያን እናስታውቃለን።

የከርሞ  ሰው ይበለን።