Tuesday, February 22, 2011

የፍርድ ቤቱ ቀጠሮ

ውድ አንባብያን እንዴት ከረማች? እኛ አሁንም የጀመርነውን ለመጨረስ ከመታገል ወደ ኋላ አላልንም። የተፈጠረ ብዙ ነገር ብንታዘብም የፍርድ ቤት ዜና ከማግኘታችን በፊት ለእትምት ላለመውጣት ወስነን ነበርና ይህንኑ ስንጠብቅ ሰነበትን። እነሆኝ በዛሬው እለት የደረሰን ዜና እንደሚጠቁመው ባለፈው ተላልፎ  የነበረው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ለ March 23, 2011 9:30 AM መቀጠሩንና ሁላችሁም መጋበዛችሁን መረዋ ማሳሰብ ይወዳል። ስለሆነም በተባለው ቀን ፍርድ ቤት ለመገኘት ካሁኑ የስራ እቅዳችሁን  እንድታስተካክሉ በድጋሜ  እናሳስባችኋለን። 

በተጨማሪ ከማንም ያልወገነ ገለልተኛ የተባለው ቤተክርስቲያናችን የአመራር አባላትና ካህናት ባለፈው ሳምንት ወደ ሂውስተን በመጓዝ ከስደት ሲኖዶስ አባቶች ጋር መገናኘታቸውን የደረሰን ዜና  ይጠቁማል። በወቅቱ በስፍራው  ተገኝተው የነበሩት አባ መልከጸዴቅ የዳላስ ሚካኤልን ወደ ስደት ሲኖዶስ መጥቶ  የቤተክርስቲያኑ አመራሮ ች በመሃከል መገኘታቸውን ከማብሰራቸውም በላይ ከዚህ በፊትም 7 ዲያቆናትን የስደቱ ሲኖዶስ ድቁና  መስጠቱን አውስተዋል። በመቀጠልም ከኮሎምቦስ የስደት ሲኖዶሱ ካህን ወደ  ዳላስ ተልከው በስራ  ላይ እንደሆኑም መጠቆማቸውን የደረሰን ዜና  ያረጋግጣል። የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ዘማርያንም የቤተክርስቲያኑን አልባሰ መዘምራን አጥልቀው ይዘምሩ እንደነበርም ለማረጋገጥ  ችለናል።

ገለልተኛ የተባለው ይህ ቤተክርስቲያናችን ማንንም ሲኖዶስ አንደግፍም ሲባል ቆይቶ ዛሬ የቦርድ አባላት በእንግድነት ከነባለቦቶቻቸው መገኘት ብቻ  አይደለም መዘመር ከቻሉ ገለልታኛነቱ እምኑ ላይ እንደሆነ እራሳችሁ እንድትጠይቁ ለናንተ  እያቀረብን መረዋ  ከዓመት በፊት ያነሳው የቦርድ አባላት እቅድ እየተፈጸመ  መሆኑን ከመታዘብ በስተቀር አልተደነቅንም። ትላንትናም ሆነ  ዛሬ ትግሉ ቤተክርስቲያኑን ተቆጣጥሮ የፖለቲካ ዓላማ  መጠቀሚያ ለማድረግ እንደሆነ የምናውቀው ነገር ፣ የተናገርነው ነገር ነበር። ትላንት ውሸት ተብለን ነበር ዛሬ  ምን እንባል ይሆን?

የወር ሰው ይበለን?

የመብት ትግላችን ይቀጥላል።