Wednesday, August 25, 2010

ትልቅ ሰው በምሳሌ ያስተምራል ቀላል ሰው በስድብ ያርቃል። ቁጥር ፵

መጽሐፍ ቅዱስ አገላበጥንና "የሚሳደቡ ብጹአን ናቸው መንገስተ ሰማያትን ይወርሳሉና "የሚል ጥቅስ ማግኘት ግን ተሳነን። የሚሳደብ ሰው የሃሳብ ድሃ የሆነ ብቻ ነው።  ባለጌ ባለጌ መሆኑን የምታውቀው በግብሩና በምላሱ ነው ይባል ነበርና። ግለሰብን በማዋረድ እናቶችን በመዝለፍ፤ በታመሙ በመቀለድ፤ በሙት ላይ በማፌዝ:የግለሰብን ስም እየጠቀሱ በማስፈራራት ትልቅነት አለ ከተባለ ትልቆቹ እነማን እንደሆኑ ደግሞ እያወቅን እየመጣን ያለን ይመስለናል። ዝም ያለ ሁሉ የፈራ የሚመስላቸው፤ የመናገር እንጂ የማዳመጥ ባህሉም ልማዱም እውቀቱም የሌላቸው ግለሰቦች ብቻ ናቸው። የሚጽፉትን በማየት ደረጃቸውን ለመለየት ደግሞበነሱ አባባል " የመንኮራኩር ፈላስፋ"መሆንን አይጠየቀምና።

ውድ አንባብያን

በፍርድ ቤት የተያዘው የይግባኝ ጉዳይ የመልስ መልስ ተሰጥቶት በቅርቡ ውሳኔውን  እየተጠበቀ መሆኑን የተቆርቌሪዎች ቡድን አባላት አብስረውናል። በስድብ የተካነውና ግለሰቦችን እያዋረደ፡ ያለው የቦርዱ ደጋፊ ነን ባዮች ድሕረ ገጽ ለከሳሾቹ ክስ መልካም መረጃን እያቀበለ ለመሆኑ በቅርቡ የምናየው ታላቅ የምስራች እንደሚኖር መረዋ ለአንባብያን መናገር ይወዳል። የማስፈራሪያና የስድብ ምንጭ የሆነው ይህ ድሕረ ገጽ የመናገር መብትን የጣሰ፤ የግለሰብን መብት የተጋፋ፤ ከመጋረጃ ኋላ  ተደብቆ ግለሰቦችን የሚያስፈራራና የብዙዎችን የመሥራት፤ የመንቀሳቀስ መብት የሚጋፋ ከመሆን አልፎ የሰው ሕይወት እንዲጠፋ  ቅስቀሳ  የሚያደርግ ለመሆኑ በተደጋጋሚ ያወጣቸው ጽሁፎችን ተንተርሶ ለፍርድ የሚቀርቡበት ሰዓት መቃረቡን ስንናገር፤ ለመብት የታገለ  ማንኛቸውም ግለሰብ ይህንንም የመታገል ግዴታ  እንዳለበት በማሳሰብ ጭምር ነው።

ማንም ግለሰብ ቤተሰቡንና ንብረቱን ብሎም እራሱን የመከላከል ሙሉ መብት እንዳለው ሁሉ፤ መንግሥትም የግለሰቦች ሕይወት አስጊ ደረጃ ላይ ሆኖ  ሲያገኘው የመከላለልና የዜጎችን መብታቸውን የመጠበቅ ሃላፊነት አለበት። በደል ሲደርስ ወደ ሕግ መሄድ አዋቂነት እንጂ የሚያሰድብ ብሎም ያልተደረገ ፈጥሮ  ስም የሚያስጠፋ  መሆን አይኖርበትም።  ማንም ከሕግ በላይ መሆን አይቻለውም። የግለሰብ መብት የሚከበረው የሌላውን መብት እስካልተጣሰ  ድረስ ብቻ ነው።  ስለሆነም በሚጻፈው የተደናገጣችሁ የቤተሰቦቻችሁና የራሳችሁ ሕይወት አስጊ ደረጃ ላይ ነው ብላችሁ የምታስቡ ሁሉ፡ ድርጊቱ ከመፈጸሙ በፊት ወደ ሕግ እየሄዳችሁ ለሕግ አስከባሪዎች ማሳወቁ ለተጀመረው እንቅስቃሴ እነደሚረዳ ልናሳስባችሁ እንወዳለን። የሕግ የበላይነት እንደሚያሸንፍ ደግሞ ምንም ጥርጥር የለንም።  

ይህንን በዚህ እናቁምና ባለፈው እሑድ የቤተክርስቲያኑን መኪና አሽከርክሮ ወደ ሂውስተን ሄዶ የነበረው የቦርዱ ተወካዮችና የእናቶች የዘማሪ ቡድን አባላት እንደተጠበቀው ከስደት ሲኖዶስ ከመጡት አራት ተወካዮች ጋር ተገናኝቶ መምጣቱንና 5 ልጆችም ከዚሁ ከስደቱ ሲኖዶስ የድቁና ማእረግ ተቀብለው መምጣታቸውን የደረሰን ዜና ያረጋግጣል። ድቁና ከተቀበሉት መሃል ሁለቱ የቦርድ አባላት ልጆች አንደኛው ለቦርዱ የመከላከያ ምስክር የነበሩት "ሕፃናትን ከፎቅ ሊወረውሩ ሲማከሩ ሰምቻለሁ" ብለው የመሰከሩት ግለሰብ ልጅ መሆናቸውን ሁኔታውን የተከታተሉት ምእመናን አውስተውናል። "የስደት ሲኖዶስን ለማምጣት የተጀመረው ትግል ፍሬ እያገኘልን ነው" የሚሉ የስደት ሲኖዶስ አላሚዎች የፖለቲካ  ድርጅቶችና ግለሰቦች ፈገግታ ቢያሳዩ እውነታ አላቸው። መረዋ  የተጻራሪዎች ትግላቸው ይህን እቅድ በሥራ ለመተግበር እንደሆነ የተናገረበት ሰዓት ውሎ ስላደረ ነግረናል ከማለት በስተቀር አልተገረምንም።

ባለፈው እሁድ በቤተክርስቲያኑ የሰበካ  ሰዓት ከባለቤቷ የተጣላች እናት ወደ ሃገር ቤት ለመላኪያ ገንዘብ አዋጡ ተብሎ ገንዘብ በመዋጣት ላይ እንዳለ ከመሃል ተነስተው "ቤተክርስቲያን አስታራቂ እንጂ አፋቺ የሆነችው መቼ ነው?" ብለው የጠየቁት እናት ጥያቄአቸው ትክክል እንደነበረ ብንገነዘብም ወዲያው የዘር ግንዳቸውን ዳሰው የተለመደ የስድብ ውርጅብኝ እንዳያወርዱባቸው ፈርተንላቸው ነበር። ነገር ግን ያካባቢው ሰፈርና የቤተክርስቲያኑ መብራት በመጥፋቱ በቶሎ ለመበተን ችለናል።መብራቱን ያጠፉት ደግሞ የከሳሽ ቡድኖች ናቸው ተብሎ መወንጀሉንም በብሎጋቸው ላይ ያነበባችሁት ጉዳይ ነው።  "የመቀበር መብታችንን የሚገፍ መንግስት ባገራችን ጣለብን" ያሉት የእለቱ አስተማሪ ካህን ከፖለቲካው ውስጥ ባይገቡ ኖሮ ትምህርታቸው መልካም ነበር። ነገር ግን የከበቧቸውን ፖለቲከኞች አስደስታለሁ ብለው ያልሆነ ስህተት ፈጸሙ ብሎ መናገር  ለወደፊቱ ትምህርት ይሆናቸዋል ብለን እናምናለን።

ውድ ወንድሞችና እህቶች

ክርስቲያን በእምነት ላይ የተመረኮዘ እንጂ በዘር የተገነባ ከሆነ መጥፎ ለመሆኑ መስካሪ አያስፈልግም።

በአንድ ወቅት ሁለት አፍሪካ አሜሪካውያንን ያየ የአራት አመት ልጅ ለእናቱ  "mommy look this N......"
ሲል እናትየዋ የተሰበሰበውን ሰው ተመልክታ   " I am sorry" ብላ መለሰች።
ይህንን የሰማ አንደኛው አፍሪካ አሜሪካዊ  "don't worry we will credit  it to the source" 
ያለውን ያጫወተን ቀልደኛው ጔደኛችን ነበር።
አይዞሽ አትጨነቂ ለህፃኑ ይህንን ማን እንደነገረው እናውቀዋለን ማለቱ ነው። በሌላ  አባባል የተማረው ካንቺ ነው ብሎ ለማለት ነው።

ልጆቹን  የሚበላ ለድሮ ድመት ወይም ውሻ ብቻ ነበር ዛሬ ግን ክርስቲያን ነን የሚሉ ሲያደርጉት ስናይ አዘንን። በውሸት ፍቅር ይመጣ ይመስል የስድብ ውርጅብኝ እያወረዱ መደምደሚያው ላይ "ወደ ክርስቶስ ቤት ተቀላቀሉ" የሚሉ ያስቁናል። እራሳቸውን እንዳታለሉ ሁሉ ፈጣሪንም ያታለሉ እንደሚመስላቸው ግብዝነታቸውን በማየታችን።

ሌላው ሳናነሳው የማናልፈው ባለፈው በምእመናን የተቌቌመውን የምእመናን እንባ አስጠባቂ ኮሚቴ አባላት ስም ዝርዝር እንዲሁ በድሕረ ገጽ ላይ ወጥቶ ተመልክተናል። ለነገሩ ይህ ባደባባይ ሕዝብ ተሰብስቦ የተቌቌመ  ኮሚቴ እንጂ የሕቡእ ኮሚቴ ባለመሆኑ የስም ዝርዝሩም እንዲሁ ያደባባይ ሚስጥር ነው። ኮሚቴዎቹ በሥራ  እየተፈተኑ ለመሄድ የተዋቀሩ መሆናቸውን እንደ እንጉዳይ የሚጠፉ ሳይሆን እንደድር የተሳሰሩ መንፈሰ ጠንካሮች መሆናቸውን ከተመለከነው መናገር እንወዳለን። "ለደህና እቃ ማስታወቂያ  አያስፈልገውም" እንዲሉ በሥራችን እንጂ በስማችን መኩራራት አይኖርብንም ብለው ያለፉትን እናንተ መተዋወቅ አለባችሁ ካላችኋቸው ለጥረታችሁ እናመሰግናለን ብለው ያመሰብኑ ካልሆነ በስተቀር "ውይ ሥማችን ወጣ ብለው እንደማያፍሩ: አንጠራጠርም። በሚሰሩትየስራ ውጤት ደግሞ  እንደምታፍሩ ቃል  ብንገባ ካየነው በመነሳት ነውና ውሸት አይሆንም።
በሚቀጥለው እትምታችን በትልቅ ዜና እንደምንገናኝ በቅድሚያ ቃል እየገባን ለዛሬው በዚሁ እንሰናበታለን።

በነገራችን ላይ ለማንኛውም በ E MAIL ልትገናኙን ለምትፈልጉ ሁሉ አድራሻችን

yetayalewnetu@gmail.com   ነው


የከርሞ  ሰው ይበለን

ቸር ወሬ ያሰማን።