Friday, January 14, 2011

የተናገርነው እየተፈጸመ በመሆኑ ትንቢተኞች ነን አላልንም።

ሰላምና  ፍቅር ለሁላችሁ ይሁን አንባብያን እንዴት ከረማችሁ።

አንድ ነገር ዛሬ ደጋግመን ደጋግመን መናገር የምንወደው ነገር አለ። መረዋ እንደ ጦማር መውጣት ከጀመረበት ሰዓት ጊዜ  ጀምሮ የዋሸነውና አንባቢዎቻችንን ያደናገርንበት ጊዜ የለም። ከጅምሩ ስንለው የነበረው ነገር በሙሉ እየተፈጸመ ስናይ ደግሞ ትንቢተኞች ነን ብለን አልተመጻደቅንም። እትምት ላይ የምናመጣውን ማናቸውንም ነገር ግራና ቀኝ ሳናገናዝብ ጽፈን አናውቅም። አጀማመራችን ለጉራ ሳይሆን ባለፈው እንዳልነው መረዋ ሞተ የምንለው ውሸት ይዞ የተነሳ እለት ነው ብለን ስለምናምን መጠንቀቃችንን ለናንተ ለማረጋገጥ ነው። ዛሬ የተለየ ዜና ይዘንላችሁ አልቀረብንም። ስትሰሙት የከረማችሁትን እንጂ። ባለፈው ሳምንት ከእትምት እንድንቆጠብ በተጠየቅነው መሰረት ቃላችንን ፈጽመናል። ያን ስናደርግ ደግሞ ለውጥ ይመጣል ብለን አስበን እንዳልነበረ ልታውቁልን ይገባል። ያ የገባንው ቃለ  ቀጠሮ  ሲያከትም እነሆ እትምታችንን ጀምረናል።

ሰሞኑን ምርጫ ለማካሄድ የቦርድ ተመራጮች ደፋ ቀና እያሉ ነው። የፖለቲካ ድርጅቶችም ይወክሉናል የሚሏቸውን ለምርጫ አሰልፈዋል። እነማን እንደሆኑ ደግሞ ያነበባችሁትና የሰማችሁት ጉዳይ ነው።አዲሶች ተመራጮች ሆነው የቀረቡት ግለሰቦች ትልቅ ሹመት የሚያገኙ መስሏቸው ተነስተው ከሆነ ትልቅ ስህተት እየተሳሳቱ ነው። እየነደደ  ባለ ቤት ነዳጅ ይዞ  መግባት እሳቱን ማፋጠን እንጂ የሚያጠፋው አይሆንም። መቃጠሉ ይሻላል የሚሉ ከሆነ ሹመት ያዳብር እንላቸዋለን።

ምርጫውን ለማስቆም ከ 60 በላይ የሚሆኑ የቤተክርስቲያኑ አባላት በፊርማ ቦርዱን እንደጠየቁም ሰምተናል። ምላሹ ምን ይሆን? ብለው የጠበቁ ካሉ አናውቅም እንጂ እኛ እንቢ እንደሚሏቸው እርግጠኞች ነበርን። እንዳልነውም የቦርዱ አባላት የተሰጣቸውን ፊርማ ወርውረው ምክንያት እየፈጠሩ ምርጫውን ማስቆም የሚችል ምንም ሃይል አይኖርም ማለታቸውን ሰምተናል። የፈራሚዎቹ አባላት ሌላ የምንጠይቀው አለን እኛ በእግዚአብሄር ቤት ተስፋ አንቆርጥም ማለታቸውንም ከተጨባጭ ምንጮች የደረሰን ዜና አብስሮናል። ሚካኤል ይርዳቸው እንላለን። እኛ ግን መብትን ማስከበር የሚቻለው በሕግ ብቻ  እንደሆነ  ከተቀበልን ቆይተናልና ከሕግ ወጪ ለውጥ እንደማይመጣ ከተገነዘብን ውሎ  አደረ። ለዚህም ነው መረዋ ክስ የመሰረቱት ግለሰቦች የመክሰስ ሱስ ይዞአቸው ሳይሆን መፈናፈኛና አማራጭ አጥተው ነው በማለት ከሳሶችን ደግፎ  የተነሳው።

ከሳሾች አባል አይደሉም ያሉ የቦርድ ተመራጮች አባል ያልሆኑትን ለቦርድ እጩ አድርገው እያቀረቡ ነው።
የአባላትን ቁጥር ለማብዛት ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አባላትን እየተዋሱ እንደሆነም እየተመለከትን ነው።
የጊዮርጊስ አስመራጭ ኮሚቴ አባል የሚካኤል እጩ የሆኑት ባለቤታቸው ጊዮርጊስ ስላልተመረጡ ተናደው ነው ሲባል አልሳቅንም ቀልዳችሁን ነው አልን እንጂ።  
በኮሚቴ አባልነት ያላገለገሉ ተመራጭ ሆነው ሲቀርቡ ምነው?  አላልንም የምናውቀውን አጠናከረልን እንጂ። የራሳችን መተዳደሪያ ሕግ ነው የሚሉት ሊሰራ የሚችለው እነሱን ከጠቀመ  ብቻ  እንደሆነ ካወቅን ውሎ  አደረ። ካልሆነ ይሻራል። 
ሚካኤል ፖሊስ ቀጥሮ የቦርድ አባላት እንዳይሳሳቱ ሃጥያት እንዳይሰሩ ለማድረጉ ደግሞ ባለፈው የተፈጠረውን  የቦረዱን አባል የሴትኛ አዳሪ አፈላማ እንደ ማስረጃ ያወሱናል ይህ ደግሞ  ቤት ሊሰብሩ የሚሄዱ ወይም ኪስ ለማውለቅ የሚሄዱ ሌቦች ለጊዮርጊስ ይሳላሉ የሚለውን አባባል ያስታውሰናል። 

ትላንት አባል ካልሆናችሁ ብለው ይናገሩ የነበሩትን ግለሰቦች ክስ ከመሰረቱት ውስጥ   አንዱ ሲመልሱ "አንድ ሰው አባል የሚሆነው እኮ መብት ካለው ብቻ ነው። እኛ ከቤተክርስቲያን በፖሊስ የተባረርነው አባል ሆነን እኮ ነው።
አትናገሩም የተባልነው አባል ሆነን ነው።
ስብሰባ  አይጠራላችሁም የተባልነው 126  አባላትን አስፈርመን  እኮ  ነው"
ብለው ሲናገሩ አድምጠን ነበር። አሁንም ያ ድርጊት ሲደገም እያስተዋልን ነው።

ሽምግሌ  የማይቀበሉ
የአባላትን ፊርማ አሽቀንጥረው የሚጥሉ
ለቤተክርስቲያኑ የምናስበው እኛ እንጂ ብዙሃን አይደሉም የሚሉ
እነሱ ከስደት ሲኖዶስ ጋር እየተነጋገሩ ከሳሾች ቤተክርስቲያናችሁን ነጥቀው ለኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሊሰጡባችሁ ነው እያሉ የሚቀጥፉ
የነሱን የፖለቲካ ሽኩቻ ይዘው መምጣታቸውን ደብቀው የሌለ ኢሕአደግ እየመጣባችሁ ነው ብለው የሚያስፈራሩ
በፖለቲካ ዓለም ማንም ፓርቲ መመሪያና መርህ እንዳለው ሳይናገሩ ከሳሾች 52 ነጥብ አስፈጻሚዎች ናቸው ብለው ሲወነጅሉ ቅር የማይላቸው።
ኢትዮጵያ ያለው መንግሥት ገንዘብ አጥቶ የቤተክርስትያኑን (የከፈሉበት ይመስል) $400,000 ለመውሰድ እየሸረበ  ነው ብለው ሊያሳምኑ የተነሱ
ትላንት ያወድሷቸው የነበሩትን ግለሰቦች አሁንስ አበዛችሁት ሲሏቸው 360 ዲግሪ ተሽከርክረው ዘራቸውን እየቆጠሩ ሲሳደቡ ቅር የማይላቸው የቦርድ አባላትና ደጋፊዎቻቸው
ማ ከማ ጋር አንሶላ  ተጋፈፈ  ብለው ሲያወሩን የነበሩ መሪዎችና ደጋፊዎቻቸው
የነፍስ ግድያ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦችን እናውቃለን በማለት ስም እየጠቀሱ የመያውቁትን ፈጥረው ያልተባለ  ቀጥለው ያሰራጩ
ያልደገፏቸውን ግለሰቦች ትዳራቸው እንዲፈርስ ሚስቶቻቸውንና ባሎቻቸውን እርጃ ውሰዱ (ተለያዩ)  ያሉ ግለሰቦች
ዛሬ  ልብ ገዝተው ፈሪሃ  እግዚአብሄር አድሮባቸው ካለ  ፍርድ ቤት ትእዛዝ ምርጫ አስቁመው የሕዝቡን ቃል ያከብራሉ ማለት ለኛ አይዋጥልንም።

ሆኖም ፊርማ ሲያስፈርሙ የከረሙት ወንድሞችና እህቶች አሁንም ቦርዱን በመጠየቅ በማነጋገር መስመር ማስያዝ ይቻላል ማለታቸውን ስንሰማ በተአምር እናምናለንና ይሳካላችሁ ብለናል።

ውድ አንባብያን በሚመጣው ሳምንት 1/23/11 እሁድ በሚደረገው ስብሰባ ላይ ሙሉ ገለጻ እንደሚደረግ የገለጹልን የመብት አስከባሪ ቡድኖች ሁላችሁም እንድትገኙ በድጋሜ ጥሪ ያደርጋሉ።

ሚካኤል ፈቃዱ ከሆነ ምናልባት የምስራች ይኖረን ይሆናል።

የሳምንት ይበለን