Tuesday, May 4, 2010

የተገፋ እንጂ የገፋ ይጸድቃል ብላችሁ እንዳታስቡ ቁጥር ፳፮

ውድ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አባላት።

በሰራችሁት ቤተክርስቲያን እንደ እንግዳ፤ በመጠየቃችሁ እንደ ወንጀለኛ፤ ለመብት በመቆማችሁ እንደ ከሃዲ፤የተቆጠራችሁ። ከመቅደስ በፖሊስ ተገፍታችሁ በፌሮ እጃችሁ ለተጠፈረው፤ ለእስራት ለተጋረዳችሁ። ለፈጣሪ እንጂ ለሰው አናጎበድድም በማለታችሁ ለተወገዛችሁ ከሥራ ለተባረራችሁ አባቶች። ለሁላችሁም ምስጋና ይድረሳችሁ።

እነሆኝ ለቅሶአችሁ የገባቸው በደላችሁ የተሰማቸው ምእመናን በዝምታ የሚደረግ የለምና ተሰብስበን መወያየት አለብን ብለው ለፊታችን ቅዳሜ ስብሰባ መጥረታቸውን ሰምተናልና ሁላችሁም በስብሰባው ላይ እንድትገኙ መረዋም ጥሪውን ያቀርባል።

በዝምታ ያተረፍነው ነገር ቢኖር ንቀትን ብቻ ነው።
ሁሉም ለመብቱ የመታገል ግዴታ  አለበት።

ቤተክርስቲያን የመንፈሳዊ ቦታ  እንጂ የፍራቻ ቦታ መሆን አይኖርበትም።

ሰው ማምለክ  የሚችለው መጀመሪያ መብቱ ሲጠበቅ ብቻ ነው።
ኑ በስብሰባው መታሰር አይኖርም።
ኑ በስብሰባው መታፈን አያጋጥማችሁም።



ለመወያየት እንጂ ለመጣላት መሰብሰብ አያስፈልግምና ለመጣላት ለመሳደብ እቅድ ያላችሁ እባካችሁ አትምጡ።



ቀኑ



5-8-2010



ሰዓት



4፡00 P M



ቦታ



Double Tree Hotel Dallas


Richardson


1981 North Central Expressway,


Richardson


TX ,75080

972 808 5386