Sunday, April 25, 2010

በጠበበው ደጅ ግቡ ..... " ማቶዎስ ም 7 ቁ 13 ቁጥር ፳፫

የማቴዎስ ወንጌል
 ምእራፍ  7 ቁጥር  13 በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው። 
14 ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።
15 የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።
16 ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?
17 እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል።
18 መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት፥ ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት አይቻለውም።
19 መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።
20 ስለዚህም ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ።

የማቴዎስ ወንጌል
 ምእራፍ 5 ቁጥር 11 ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።
12 ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና።

13 እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም።
14 እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።
15 መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል።
16 መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።

ወንድሞችና  እህቶች የቤተክርስቲያን አባላት።   ከዚህ በላይ ያሉትን ጥቅሶች ማንም አልነገረንም በሚካኤል ስም እንመሰክራለን ነገር ግን የገጠመንን የቤተክርስቲያን ችግር አሰብንና እስቲ መጽሐፍ ቅዱስ እናገላብጥ ብለን ስናገላብጥ ያገኘነውን እንዳለ  አቀረብነው። ስለ እውነት ቃሉ ልባችንን ነካው። የናንተንም ይነካው ይሆናል  ብለን እንዳለ  አቀረብነው። መላከ ሳህልን በቅዳሜ እለት ከቤተክርስቲያን ያባረረው ቦርድ ያባረረው ካህኑን ብቻ  ሳይሆን ሁላችንንም ነው። በፖሊስ ታጅበው ሁለተኛ ቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ እንዳይገቡ የተነገራቸው አባት ጥፋታቸው ቦርዱን እንደ እግዚአብሐር አላመልክም  ማለታቸው ብቻ ነው። የቤተክርስቲያንችን መተዳደሪያ ደንብ አንድም ሰው ቤተክርስቲያን መጥቶ  የማምለክ መብቱ አይገፈፍም እያለ  6 የቦርድ አባላት ብቻቸውን ወስነው የሃገሩን ሕግ የማያውቁትን ካሕን አስፈራርተው ማባረራቸው የሚያሳዝን ነው። ተናጋሪው አቶ  አበበ ጤፉም ሆኑ እንደስእል የተቀመጡት ሊቀመንበር የቤተክርስቲያኑን ትግል ወደፊት ወስደውታል። ካሁን በኋላ  የቤተክርስቲያኑን ገንዘብ በመጠቀም ሁላችንም ላይ አደጋ  እንዳይፈጥሩ መዘጋጀት የግድ ይላል።

ሕግ የማያውቁ ሕግ አስፈጻሚዎች የሆኑ የቦርድ አባላት በካሕኑ ቤተሰብ ላይ የወሰዱት ብያኔ  እነሱ ላይ እንደሚዞር ምንም ጥርጥር የለንም። ከኋላ  ሆነው ይህ እንዲደረግ ይጥሩ የነበሩ ግለሰቦችም እራሳቸውን ቢገመግሙ መልካም ነው እነላለን። የተደረገው ድርጊት አንድም የመንፈስ ነገር የለበትምና። በሕዝብ ገንዘብ አባላትን ማጎሳቆል መቆም አለበት። ለዚህም ፈሪሃ  እግዚአብሔር ያደረበት ሁሉ መጠየቅ ያለበት ይመስለናል።

ቀሲስ መስፍን ከሰበካ በኋላ  ያለቀ  ባትሪ ሆኛለሁና ካሁን በኋላ  አልቀጥልም ብሎ  መሰናበቱን ስንሰማ  በድጋሜ ሐዘን ተሰማን። 
ወንድሞች በዛሬ  ደስተኛ የነበሩት የቆዩት ካህን ከነልጃቸው ሊሆኑ ይችል ይሆናል። ዛሬ የሚጨፍሩ ነገ  እንደሚያዝኑ ግን ምንም አንጠራጠርም። ቦርዱ የፖሊስ መአት ያሰለፈው ለምን ነበር?  ቤተክርስቲያን በክርስቶስ እንጂ በፖሊስ ትጠበቃለችን?  ወንድሞ ቼ የፖሊሱን ጋጋታ አይታችሁ "እኔ  ቤተክርስቲያን እንጂ ፖሊስ ጣቢያ አልሳለምም "ብላችሁየ የተመለሳችሁ ስንቶቻችሁ ናችሁ? 
ይህንን የጠየቅነው የተመለሰውን ሕዝብ በማየታችን ነው። ነገ ወረቀት የሌላቸው አዲስ የመጡ ቢኖሩ ፖሊስ ፍራቻ ወደቤተክርስቲያን እንዳይደርሱ እየተደረገ ነው። በነገራችን ላይ ሁላችንም እንዴት የመኖሪያ ፈቃድ እንዳገኘን እንተዋወቃለን።
ፖለቲከኞች ዛሬ ተሸነፉ እንጂ አላሸነፉም።
የቦርድ አባላት በሚያስደንቅ ሁኔታ  ዛሬ ተሸነፉ እንጂ አላሸነፉም።
የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች ዛሬ  ተሸነፉ እንጂ አላሸነፉም።
ያሸነፉት ሚካኤል ፍርዱን ይስጥ ያሉት ናቸው። አምላክ ልጁን እንደሰጠን ሁሉ ዛሬም ሁለቱን ልጆቹን አሳልፎ ሰጠን። መከተልና ክርስቲያናዊ ግዳጅ መወጣት የሁላችንም ፋንታ ነው።
ባለፈው አጠቃላይ ስብሰባ አቶ  ሰይፉ ካሳና ዶክተር ሰሎሞን ስብሰባውን ለመካፈል መጥተው መከልከላቸውን ስንሰማ አልተደሰትንም። በሰፈሩት ቁና  ማለት እንችል ነበር ግን ቤተክርስቲያን ሆነብን።

ትግላችን በተጠናከረ  መንገድ ይቀጥላል።ቤተክርስቲያን የአማንያን ትሆናለች።