Wednesday, October 6, 2010

ተከሳሽ የከሳሽን መልስ ቢያውቅ ኖሮ ፍርድቤት አይደርስም ነበር ቁጥር ፵፬

እንኴን አደረሳችሁ ውድ አንባቢዎቻችን።

መስቀል አለፈ፣ እኛን ገና አልሰቀሉንም።
ስም አጠፉ መሰላቸው እንጂ አልጎዱንም።
የስድብ ውርጅብኝ አወረዱብን ስንንበረከክ አላዩንም።
የከሳሾችን ጠበቃ ሳይቀር በማያውቀው ቋንቋ ተሳደቡ አዋረዱት ስሙን አጠፉ ከክሱ እራሱን ሲያገል አላስተዋልንም።
ከትላንት በስትያ በብሎጋቸው የሰደቡትን ባለፈው ሰንበት ተቀጠረ የተባለውን አስተማሪ እንዲሁ በብሎጋቸው ሲያወድሱት "ስንሰማ ባንድ አፍ ሁለት ምላስ" አልን እንጂ አልተገረምንም። {ትላንት በመረዳጃ  ማሕበሩ የተደረገውን የኢትዮጵያን ቀን አስመልክቶ የተረኩትን  መልሰው የሻርሩትን ባለፈው መረዋ አስነብበናችሁ ነበርና} የሚገርመን ምን እንደሚፈልጉ አለማወቃቸው ብቻ  ነው።
በፖሊስ ያሳሰሯትን ወጣት ለልጆቿ ምን? እንዴት እንንገራቸው?  ብሎ  እንደመጨነቅ በቁርባን ያገባችውን እናት ሃይማኖት የሌላት እያሉ ሲሳደቡ አነበብን።  ስለዘለፏት የምትሸማቀቅ ከመሰላቸው እምነታቸውን መጠየቅ ያለባቸው እነሱ መሆን አለባቸው እንላለን። ትላንት ዘሯን ቆጥረው የፖለቲካ  ሴት ናት እንዳላሉ ዛሬ ትክሰሳ የምትከሰው ኢንሹራንሱን ነው ብለው ቅራኔውን ለማስፋት ተራወጡ። ወንድሞችና እህቶች ባለፈው እንዳልነው ቤተክርስቲያን የአማንያን እንጂ የተወሰነ ዘር ንብረት ነው ማለት ወንጀል ባይሆን እንኴን ክርስቲያናዊ አይደለም። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ደግሞ የሃይማኖቱ የመጀመሪያ ተቀባይ የነበረው የትኛው ክፍል ነበር?

የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ  ልሳን የሆነው ብሎግ WWW.MELEKET4U.BLOGSPOT.COM ያወጣውን ኮሚቴው ከሽማግሌዎች ጋር አድርጎት የነበረውን ውይይት ሃሰት ነው ሲሉ አነበብን። ነገ ደግሞ  እነ አቶ በተሩ እነ ዶክተር ታየ እነ አቶ ጌታቸው እነ አቶ ኪዳኔ እነ አቶ  ግርማቸው እነ ሻለቃ ተፈራ እነ ወይዘሮ በየነች እነ አቶ ደም መላሽ የሚባሉ ሰዎች በዳላስ መኖራቸውን አልሰማንም ቢሉ አትገረሙ። ከመሰላቸው ይዋሹ መዋሸት ደግሞ በሽታ  ነው የሚላቸው ጓደኛ እንደሌላቸው ስናይ ማዘናችን ግን አይቀርም። ምንም ቢሆን ወንድሞቻችን ናቸውና።

በሌላ ወገን የምንነግራችሁ ነገር ቢኖር በነገው እለት ከጠዋቱ 9:00 ሰዓት ላይ የፍርድ ቤት ቀጠሮ እንዳለ  ነው።  የተያዘው ቀጠሮ  ቦርዱ ለከሳሽ ጠበቃ ተጠይቆ አልሰጥም ያለውን መጠይቅ ዳኛው ትእዛዝ እንዲሰጥበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ቀደም ባለው የመጀመሪያው ቀጠሮ ላይ የቦርዱ ጠበቃ የተነሳው ቪዲዮ በመረጃነት አይገባብኝም ምስክር አይሰማም ብሎ የተከራከሩት በዳኛው ውድቅ መደረጉ የሚታወስ ነው።ዳኛው ይህ ክስ የመብት እንጂ የሃይማኖት ጉዳይ ምንም እንደሌለው ከመናገራቸውም በላይ ቪዲዮውም እንደመረጃ እንዲገባ  ምስክርም እንዲሰማ ማድረጉ ግልጽ ነው። የተከሳሽ ጠበቃ ተቃውሟቸው እንዳልሰራ ሲረዱ ፍርድ ቤቱን ሌላውን የፍርድ ቤት ክስ ያየው ዳኛ ይህንንም በተጨማሪ ይመልከትልን ምክንያቱም ጉዳዩን በሌላ መልኩ አይቶታልና ብለው በጠየቁት መሰረት፣ ዳኛውም የቀድሞውን ዳኛ አነጋግረው ፈቃደኛ ከሆነ ቢዛወር እንደማይቃወሙ ቃል በገቡት መሰረት ምን አልባት የቀድሞው ዳኛ ይህንን ለማየት እፈልጋለሁ ካሉ ሊተላለፍ እንደሚችል ጉዳዩን ከተከታተሉት ግለሰቦች መረዳታችንን ልናሳውቃችሁ እንፈልጋለን።  ይህ ክስ አባላትን ማባረር ከጀመሩ በኋላ የተመሰረት መብትን ለማስከበር የተመሰረት ክስ መሆኑም ለሁላችንም ግልጽ ነ ው።
ስለሆነም በነገው እለት ምንም ተፈጠረ  ምን
መተዳደሪያ ደንቡ ወደነበረበት ካልተመለሰ 
የተባረሩ አባላት ካልተመለሱ
የአባላት ክፍያ  ወደነበረበት ካልተመለሰ
አንዱ ልጅ ሌላው እንጀራ ልጅ መሆኑ ካልቀረ
የአባላት መብት ካልተጠበቀ
ፖለቲከኞች ከቤተክርስቲያን ውስጥ ፖለቲካቸውን ካላቆሙ
የምእመናንን ጥቅም አስከባሪ ቦርድ እስካልተቋቋመ
ብሎም
ባለፈው እንዳደረጉት ቦርዱ በመሰብሰቢያ አዳራሻቸው እነ አቶ ሃይሉ እጅጉን ጠርተው እየተሳደቡት ክስ ከመሰረቱት ውስጥ ነህና ካላረፍክ እንከስሃለን የክስ አጋሮችህንም አብረን ለፍርድ እናቆማለን እንዳሉት በተናጠል ማስፈራራት እስካላቆሙ ድረስ 
በቦርዱ ብሎግ መሳደባቸውን እስካልገቱ ድረስ
መታገላችንን  አናቆምም

ዳላስ ለመኖር ደግሞ  የቦርድ ደጋፊዎች ነን ባዮችን ፈቃድ አንጠይቅም።
ሚካኤል ለተገፉ እንጂ ለገፊዎች ይቆማል ብለን አስበንም አናውቅ።
የነገ ሰው ይበለን።