Saturday, October 30, 2010

ከሰገነት ያለ ሰው እይታው ሁል ጊዜ ቁልቁል ነው ቁጥር ፵፮

እንዴት ከረማችሁ ላላችሁን ሁሉ ሰላሙን ያድላችሁ እያልን ከልብ ለሚያበረታታው የ E MAIL መልክታችሁ  አሁንም  በምእመናን ስም ምስጋና እንድናቀርብ ፍቀዱልን። የፈጣሪና የእናንተ እርዳታ ባይታከልበት ኖሮ እዚህ እንደማንደርስ መናገር ደግሞ እውነት ነው። በመሃከሉ የራስም የሕይወት ትግል ያዘንና ስንሯሯጥ ከረምን።ያም ሆኖ አዲስ የተከሰተ ነገር ባለመኖሩ "ከቤተክርስቲያኑ ሱቅ ሰራተኞች መባበር"  ሌላ እሱንም ባለፈው የተናገርነው መሰለን፡ ብዙ ያጋጠመን የለም ለማለት ነው። መረዋ የናንተ ነውና የሰጣችሁንን ምክር በመቀበል አሁንም በከፍታው ላይ ለመራመድ ቃል እንገባለን።

በምንም ዓይነት እረግረግ ውስጥ ገብተን በቆሻሻ ዋልካ ተጨማልቀን፡ በስድብ ተበሻቅጠን አታዩንም።
በምንም ዓይነት በመብታችን ተደራድረን በፍራቻ አጎብድደን አታስተውሉንም።
በምንም ዓይነት ከመልአኩ እግር ሥር እንጂ ከግለሰብ እግር ሥር ወድቀን አታዩንም።
በምንም ዓይነት ለፈጣሪ ካልሆነ  በስተቀር ለግለሰብ አናጎበድድም።
በምንም ዓይነት ለፍቅር እንረታለን እንጂ ለጥላቻ አንበረግግም።
በምንም ዓይነት የሚያከብሩንን እናከብራለን እንጂ አንፈራም። ስለሆነም እናንተው እንዳላችሁት " ለሚሳደቡ ጸልዩላቸው" ለሚታገሉ እንዱሁ ለብርታታቸው ሁሌ በጸሎት አትርሷቸው።

አንድ መንፈሳዊ አባትን አንዱ ምእመን አባቴ ዋና የሚያጸድቅ ነገር ምንድነው? ብሎ  ለጠየቃቸው ሲመልሱ "የሚያጸድቀው ለማድረግ የሚከብደው ነገር ነው። የሚያስኮንነው ግን በየቀኑ የምታደርገው ቀላሉ ነገር ነው" አሉት። እንዲያ ካሉ እግዚአብሔር የለም ማለት እኮ ቀላል ነው አላቸው። እሳቸውም "አሁን የሲኦልን ቁልፍ አገኘኸው"  አሉት።   ሰውን መግደል እኮ  እንደዚሁ ቀላል ነው ሲላቸው "አሁን ደግሞ  የሲኦልንም የዘብጥያውንም ቁልፍ ተረከብከው ማለት ነው" አሉት ይባል ነበር።

ባጋጣሚ ሰሞኑን የቀድሞ ፕሬዚዳንት የነበሩትን የቢል ክሊንተንን MY LIFE  "ሕይወቴ"  የሚለውን  መጽሐፍ ስናነብ ያየነውን እናካፍላችሁ። ፕሬዚዳንት ክሊንተን ሁለተኛ ደረጃ  እንደገቡ የጻፉትን ድርሰት አስታውሰው ሲያስነብቡ (PAGE 58) ......."I, ME, MY, MINE........ THE ONLY THINGS THAT ENABLE WORTHWHILE USES OF THESE WORDS ARE THE UNIVERSAL GOOD QUALITIES WHICH WE ARE NOT TOO OFTEN ABLE TO PLACE WITH THEM - FAITH, TRUST,LOVE, RESPONSIBILITY, REGRET, KNOWLEDGE." ብዙ ጊዜ አናደርገውም እንጂ እኔ በግሌ  የኔ የግሌ ........የሚሉትን ቃላቶች ከአምልኮ ከእምነት ከፍቅር ከሃላፊነትመቀበል ከቁጭትና ከእውቀት ጋር ብናጣምራቸው አለማቀፋዊ ስምምነት ያለው መልካም ምግባር ይሆን ነበር። ትርጉም የራሳችን።

ይህንን ያነሳነው እያንዳንዳችን ያደረግነውን መጠየቅ ብንጀምር ስህተትን ለማረም ይረዳ ነበር ለማለት ያክል ነው።

ሚስቴ ለምን ፈታችኝ ከማለት ይልቅ? ምን ብበድላት ነው የተጣላችኝ? ማለት የተለያየ ትርጉም እንዳለው ሁሉ የተለያየ መፍትሄ  ላይም ይጥላል።

ይህንን ካልን ዘንዳ ወደ ጉዳያችን ስንመለስ ባለፈው በ DECEMBER ወር ተቀጥሮ  የነበረው ቀጠሮ አሁን ወደ 192 ፍርድ ቤት በመዛወሩ ዳኛው ካላቸው የቀጠሮ ቅደም ተዋረድ ጋር በማዛመድ ለJANUARY 10 2011 ለክርክር  መቀጠሩን ስንነግራችሁ፡ ሌሎች እንዳስፈራሩን መንፈቅ ሳይሆን አንድ ወር ብቻ በመራዘሙ ደስተኞች መሆናችንን በመግለጽ ጭምር ነው። ፍርድ ቤት ለችግራችን ሙሉ ለሙሉ መፍትሄ ይሰጣል ብለን አስበን እንደማናውቅ ሁሉ መብታችንን እንደሚያስከብርልን ግን ለሴኮንድም ተጠራጥረን አናውቅም።

ለእምነቱም እኮ  መብት መኖር አለበት
ለማስቀደሱም መቆሚያ
ለማስጠመቁም ማጥመቂያ
ለማስፈታቱም መጠጊያ  ሲኖር ነው።


እናት ሃገር ቢሞት ባገር ይለቀሳል
አገር የሞተ እንደሁ ወዴት ይደረሳል ያለውን ያስታውሷል።

አንዴ በደርግ ዘመን መሆኑ ነው ባለቤቷ ፊቱን እያዞረ ያስቸገራት ሚስት ወደቀበሌ ሄዳ ችግሯን ለቀበሌ ትናገራለች። ቀበሌም ሁኔታውን አዳምጦ ባልየው ፊቱን ሁልግዜ  እያዞረ  መተኛት እንደሌለበት ይነገረውና ትእዛዙን ተቀብሎ ማታ ሚስቱን አቅፎ ያድራል። በነጋታው ካሁን በኋላ  አላደርገውም ብሎ ለሚስቱ ሲነግራት ባለቤቱ "ወደህ በቀበሌ ተገደህ" ብላ አለች ይባል ነበርና እኛም ለጊዜው በቤተክርስቲያን ማስቀደስ መቻላችን በሕግ ግዳጅ እንጂ ተወርውረን ተጥለን እንደነበር ለመጥቀስ ያክል ነው። ማንም ለማስቀደስ የቦርዱን ቡራኬ  ማግኘት ይኖርበታል ብለን አናምንምና። እዚህ ቤተክርስቲያን ደግሞ  ከዚህ በፊት እንደተናገርነው አንዱ ልጅ ሌላው የእንጀራ ልጅ ሆኖ መቀጠል አይቻልም። ሁሉም እኩል ነው ማለት እስካልተቻለ  ድረስ ደግሞ ትግሉ ይቀጥላል። ለአምልኮ ቡድን የሚያስፈልግበት ምክንያት አይታየንም። እንዴውም ቤተክርስቲያን ዘመድ ለሌለው ብቸኛ ለሆነ አልነበረም እንዴ?
በቅዳሴ ሰዓት ከሰገነት ተቀምጠው ቁልቁል በማየት ንቀት የለበሱ ካሉ ማንጋጠጥ መልመድ አለባቸው እንላለን። ካልሆነ መጨረሻው አያምርምና። አቶ ሃይሉ እጅጉን ጠርተው እንከስሃለን ብለው የተሳደቡ የቦርድ አባላት። ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ለሚያደርጉት ሥራ  ሁሉ በግል ተጠያቂ እንደሚሆኑ የዘነጉ ይመስላል። ባለፈው በደጋፊዎቻቸው ብሎግ ላይ እንዳሉት እኛ ምን እንሆናለን የመድሕን ድርጅቱ ይጨነቅበት ማለት አይቻልም። እዚህ አገር ደግሞ  እንኳን የዚህ የቤተክርስቲያን የቦርድ አባላት ቀርቶ የአሜሪካዊውም ፕሬዚዳንቱም ካጠፉ ፕሬዚዳንት ነኝ አልጠየቅም ማለት አይቻላቸውም። የኒክሰንን የዋተር ጌት ቅሌት ያስታውሷል። ማንም በድርጅት ሽፋን ተነስቶ  ምእመናንን መተናኮል አይችልም ለማለት ነው። ይህንን ስንል ደግሞ ለማስፈራራት ሳይሆን በመብታችን ላይ ለደረሰው በደል ተጠያቂዎች እንዲጠየቁ ለማድረግ እንደምንታገል ለመግለጽ ጭምር ነው።

ለተሳዳቢዎቹ ሰው ላንመስላቸው እንችላለን እኛ ግን ሰው መሆናችንን እያወቅን ላላወቁ ለማሳየት በሕግ እንታገላለን።

በቅርቡ ቸር ወሬ እንደምንሰማ እርግጠኞች ነን።

ለዛው ያድርሰን

ልትገናኙን ለምትፈልጉ አሁንም አድራሻችን

YETAYALEWNETU@GMAIL.COM  ነው። መልካም ሳምንት።