Friday, February 12, 2010

ይሉኝታ የሚሰማው መጭውን ማየት የሚችል ብቻ ነው። ቁጥር ፲፪

ከቁልቋል ወተት ሙጫ እንጂ ቅቤ እንደማይወጣ ሁሉ ተመረጡ ከተባሉት አዲስ የቦርድ አባላት ለውጥ ይመጣል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው ብለን እናምናለን። ለመሆኑ ይህንን ሁሉ ችግር የፈጠረው ማን ሆነና?። ምእመናን መባረር አለባቸው ብለው ያባረሩ እነሱ፤ በፖሊስ መመንጠር አለባቸው ያሉት እነሱ። ሕጉን ካልቀየርን ብለው የተነሱት እነሱ። የቤተክርስቲያኑ አባላት እንደማያጸድቁት ሲያውቁ በስልጣናችን ሕጉን ቀይረናዋል ያሉት እነሱ። ሕጉ ከመቀየሩ በፊት የክፍያ ተመን የወሰኑት እነሱ። ዛሬ የቦርድ አባላት ሆነው የተመረጡት እነሱ። ብለን ለመጠቆም ያክል ነው።
አባላት $30 ብር መክፈል አቅቷቸው መክፈል ያቆሙ ከመሰላቸው በጣም ተሳሰተዋል። የቦርዱ ተመራጭ ዶክተር መክፈል ከቻሉ ማንም መክፈል ይችላል። የቦርዱ ተመራጭ ዶክተርም ሆኑ አቶ አበራ ቤተክርስቲያናችንን ከመቀላቀላቸው በፊት አባላት ምን ይከፍሉ እንደነበር ቤተክርስቲያኑ በስንት ጊዜ ተከፍሎ እንዳለቀ እጎናቸው ያሉትን አዲስ ሊቀመንበር ጔደኛ እህ ቢሉ የሚነግሯቸው ይመስለናል። ነገሩ ከዛ በላይ የእምነትና የተቃውሞ መግለጫ መሆኑን ግን የተረዱት አይመስልም። ድኩላ አይቶ ለማደን የሚዘል ነብር በመሃከል ጉድጔድ መኖሩን ቢረሳ አይገርምም እይታው ድኩላው ላይ ነውና። አንተዬ የቆየ አባባል ትዝ ይልሃል "ጔደኛህ ማን እንደሆነ ንገረኝና ማን መሆንክን እነግርሃለሁ" ይባል አልነበር። ታዲያ ማንና ማን እንደተቀናጁ አስተውለን ወዴት እየሄዱ እንደሆነ መናገር ምን ያዳግታል። አቶ አበራ የቤተክርስቲያን "ተቆርቌሪ" አቶ ምናሴ የቤተክርስቲያን "ጠላት"። የሂሳብ ከፍሉ ዶክተር ቤተክርስቲያን "ገንቢ" ዲያቆን አርአያ ቤተክርስቲያን "አፍራሽ":: ሰሎሜ "ፍጹም ክርስቲያን" ጥሩአየር "አስመሳይ አማኝ":: ከዚህ መመሳሰል ላይ ችግር የለም ካልን ሁላችንም ሃኪም ማየት ሊኖርብን ነው። "ንስሐ" የሚለው ቃል አያስፈራንም ብለን ስላመንን ነው ለመጠቀም የተቆጠብነው።
"በላበክ ቴክሳስ የፕሮቴስታንት ተከታይ ሆነው የከረሙት ዶክተር ትላንት መጥተው ቤተክርስቲያናችንን አፈራረሱት" የሚባለውን አባባል ከማይጋሩት አንዱ መረዋ ነው። ተጠያቂዎቹ የጠቆሟቸውና ለስልጣን ያበቌቸው አባላት ናቸው ብሎ ስለሚያምን። ዶክተሩን ምረጡ ይሉ የነበሩ ግለሰቦች ዛሬ ዶክተሩ ጉድ አደረጉን ቢሉ የሚያታልሉት እራሳቸውን ብቻ ነው። የራሳችንን ድክመት ለመሸፈን ሚካኤል ታምር ያሳየናል ማለትስ የራስን እምነት ፈተና ውስጥ መጣል አይሆንምን? ሚካኤልማ ምን እያደረጉ እንደሆነ እያሳየን ነው እያየን የታወርነው እየሰማን የካድነው እኛ ነን እንጂ። አቶ እዩኤል ከስልጣን ይገፈተራሉ ብለን ስንናገር ሕልም አይተን አልነበረም፡ የሁኔታዎችን አካሄድ በማየት እንጂ። ገንዘብ አጎደሉ የተባሉት እንደገና በገንዘብ ላይ ይሾማሉ ያላልነው ግን ምንም አባላትን ቢንቁ እንዲህ አፍጥጠው ይወጣሉ ብለን ስላልጠረጠርን ነው። ይህንን ባለማየታችን እራሳችንን ልንወቅስ እንወዳለን።
በየድግሱ ሲጋበዙ የነበሩት ዶክተር ዛሬ ጋባዡ መጥፋቱ ያስጨንቃቸዋል ብለን አስበን ነበር። አሁንም ተሳስተናል። የሳቸው ሕልም ሌላ ነውና። ሲያዙአቸው የነበሩትን የቀድሞ ሊቀ መንበር አንቅሮ ለመትፋት ሰከንድ ያልፈጀባቸው ዶክተር ከአዲሱ ሊቀመንበር ጋር ለወራት ይቆያሉ ብለን አናምንም አዲሱ ሊቀ መንበር ምንም መሃይም ቢሆኑ ፈጣሪን ይፈራሉ ብለን በመገመት። የዛሬውን ሊቀመንበር ምንም ባለቤታቸው ቢቆጧቸው በመቆየት የሕዝቡ ፊት ግርፊያ ያንበረክካቸውና "ምነው ወሎ" ብለው ድንገት ይነሣሉ ብለን መተንበይ እንወዳለን።
መረዋ ሰሞኑን ከሰበሰበው መረጃ አንዳንዱን እናካፍላችሁ።
ባለፈው አጠቃላይ ስብሰባ ላይ ሊቀ መንበሩና በወቅቱ የሂሳብ ተቆጣጣሪ የነበሩት ወይዘሮ ገንዘብ እንደጎደለ መጠቆ ማቸው ይታወሳል። በዚህም ምክንያት ቤቱ ይህንን የሚያጣራ ኮሚቴ መሰየሙም የሚታወስ ነው። ቤቱ ከሰየማቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ አቶ ኪዳኔ ምስክር እንደነበሩ ዘጋቢዎቻችን ጠቁመው፡ ይህ ግን አቶ አበራንም ሆነ ዶክተሩን ስላስቆጣቸው በቦርድ ስብሰባ ላይ ነገሩን አንስተው አቶ ኪዳኔ ምስክር ከኮሚቴው ባስቸኴይ ተገፍትረው እንዲባረሩ በድምጽ ብልጫ አስወስነዋል። "ይህ የቤቱን ስልጣን መጋፋት ይሆናል ምክንያቱም የተመረጡት በምልአተ ጉባኤው ነው" ቢባሉም አሻፈረን መተዳዳሪያ ደንቡ ደግሞ ቦርዱ የቤቱን ውሳኔ መሻር ይችላል ስለሚል መሻር እንችላለን። በተጨማሪም የአቶ ኪዳኔ ባለቤት ቤተክርሰቲያኑን የከሰሱ ስለሆነ አቶ ኪዳኔ በሚስታቸው ወንጀለኛ ናቸው መባሉንም ልናወሳችሁ እንወዳለን። እንደተለመደው መራጩ የቤተክርስቲያን አባል አላዋቂ ነውና አቶ ሙሏለም ይወስኑለት ተብሏል ማለታችን ነው። በዚህ አጋጣሚ ለአቶ አበበ ጤፉ ኧረ ድንበር እየተጣሰ ነው ብለን "አቤቱታ" እናቀርባለን። በሌላ ዜና selam tewahedo እንዲመስል ከ H ቀጥሎ ያለችው E የሌለችበት BLOG ብቅ ብሎ መጥፋቱን ስናበስራችሁ ይህ የሚደረገው ትክክል አይደለም የሚሉትን ግለሰቦች በስም እየጠቀሰ በመሳደብ ሴራቸውን አከሸፍነው የሚለው ጽሑፍ ለምን ባጭር ጊዜ ውስጥ እንደተነሳ ባይገባንም በላዩ ላይ ቁምነገር ስላልነበረበት አፍረው ሊሆን ይችላል ብለን ተቀብለነዋል። ጽሑፉን ማየት ለምትፈልጉ ሁሉ ጥያቄአችሁን E mail ብታደርልን ልንልክላችሁ ዝግጁ ነን።
በሌላ ዜና ሰሞኑን የቤተክርሰቲያኑ አካሄድ ያላማራቸው ግለሰቦች እያደረጉ ያለውን ንቅናቄ መረዋ በሙሉ ልብ እያደነቀ ከጎን ሆኖ ለመስራትም ፈቃደኛ መሆኑን ቃል መግባት ይወዳል። ወንድሞችና እህቶች የቤተክርስቲያኑን ገንዘብ ስለያዙ አሸነፍን ብለው የሚኩራሩትንና ተቃዋሚ ነው የምንለውን መንጥረን እናባርራለን ብለው የተማማሉትን እነሱ እኛ ባዋጣነው ገንዘብ ይመኩ እኛ ደግሞ በእምነትና በህብረት እንቌቌማቸዋለን። ምን ግዜም በእውነት ላይ የተመሰረተ ስብስብ አለት ሆኖ ይከርማልና። ለእምነትና ለእውነት እንቁም። በክርስቶስ እርዳታ ቤተክርስቲያን ታሸንፋለች።