Sunday, February 28, 2010

የጋቢን ጥቅም ያላወቀ በልቃቂት ይጫወታል ቁጥር ፲፭

እንዴት ከረማችሁ እድምተኞቻችን። ሰሞኑን እየተከሰተ ያለውን የድህረ ገጽ የጽሑፍ ፍልሚያ ያየ ሰው ወይ ጉድ ማለት ሳይሆን ምን ዘመን ላይ አደረሰን? ቢል የምንረዳው መሰለን። የዳላስ የቤተክርስቲያን ብጥብጥ የሃይማኖት ሳይሆን የፖለቲካና የጥቅም ከሆነ ውሎ አደረ። የሃይማኖት ቢሆን ኖሮማ እስካሁን ችግሩ ተፈቶ ነበር። ፈሪሃ እግዚአብሔር ያደረባቸው ምእመናን ይቅር ለእግዚአብሔር ለመባባል ችግር የለባቸውምና። ስዚህም ነበር መረዋ በመደጋገም ችግሩ የመብት መገፋት: የንዋይ ጥማት: የፖለቲካ ክስረትና ፍጭት ነው እንጂ የሃይማኖት አይደለም ብሎ ከደመደመ የሰነበተው። በተደጋጋሚ ሰሞኑን እየተሰራጩ ያሉት የተለያዩ Bolgs ላይ የሚጻፉትን ጽሑፎች በማንበብ ጸሐፊዎቹ ከየትኛው ወገን እንደሆኑ ምን እንደሚፈልጉ ለመናገር እንደሚቻል የገመገምንበት ሰዓት ነበር። መረዋን የምናዘጋጅ ግለሰቦች ከፈጣሪ በስተቀር ማንንም እንደማንፈራ ደጋግመን ግልጽ ያደረግን ይመስለናል። ወንድምና እህትን ከማክበር ግን ወደኋላ ያልንበት ሰዓት የለም ወደፊትም አይኖርም። የሚፈራ ሰው የእምነት ክስረት ያለበት ብቻ ነው። ስለሆነም መረዋ የማንንም ስም አስመስሎ ለማታለል ብሎም የበግ ለምድ ለብሶ የሚደበቅ ተኩላ ለመሆን እቅድ የለውም። ሰሞኑን የመረዋን ስም አስመስለው በ blog ላይ ሊያወናብዱ የተነሱትን አስመሳዮች ይህ ሌላውን የሚያታልሉበት መስመር ከመሰላቸው ይግፉበት ከማለት በስተቀር አንለምናቸውም። አባላት ደግሞ ከጽሑፋችን ማ ምን እንደሚል ስለሚያውቁ ግለሰቦቹ የሚሞክሩት ሙከራ የመጨረሻ የክስረት ደረጃ መሆኑን ያሳይ እንደሁ እንጂ የትም እንደማይወስዳቸው በእርግጠኝነት መናገር እንችላለን።
ይህ የቤተክርስቲያን ግጭት እንደተፈጠረ በድብቅ ወረቀት መበተን የጀመሩት እነዚሁ ዛሬ "የቤተክርስቲያኑን አመራር ተረክበናል" የሚሉት ግለሰቦች እንደነበሩ ምእመናን የሚያስታውሱት ጉዳይ ነው። ለበተኑት ወረቀት ምላሽ ደወል በሚል የሚታወቀው የከሳሾችን አቌም የሚያስተጋባው መጽሔት መበተን ሲጀመር እውነቱ እየመረራቸው በመምጣቱ ወደ ቦርድ ሄደው የሙጥኝ በማለት ፋታ አሰጡን ብለው "ወረቀት በቤተክርስቲያን ግቢ መበተን ተከልክሏል" የሚል አዋጅ በቦርድ አባላት አሳወጁ። ያም ሆኖ እነሱ የማይረባውን ያሉባልታ ወረቀታቸውን መበተናቸውን ቀጠሉ።
ምን እየጻፉ እንደነበር የምታውቁት ያነበባችሁት ስልሆነ ወደኋላ ተመልሰን የናንተን ጊዜ በማይረባ ማቃጠል ስለማንወድ እንዳለ እናልፈዋለን። ቆየት ብለው ደግሞ SENBETE በሚል ስም Blog ፈጥረው የስድብ አለንጋ ሲያወርዱ ያላዋቂ ሳሚ........ የሃይማኖት ሰበካ ሲሰብኩ ከረሙ።ለናሙና ስለ ሲኖዶስ ሰሞኑን ያወጡትን ገብታችሁ አንብቡላቸው። እኛ አይተን ይቅር በላቸው እያልን እየጸለይንላቸው ነው። አለማወቅ ወንጀል አይደለም። የማያውቁትን የሃይማኖት መቀባጠር ደግሞ በመምድር መናቅን ከሰማይ ደግሞ ቅስፈትን እንደሚያመጣ ግን እናውቃለን። ይህ አካሄዳቸው ሕዝቡን ለማወናበድ በማሰብ ያቀዱት ጅምር መሆኑን የተገነዘቡ ነገሩ ያሳሰባቸው ግለሰቦች Selam-tewahedo.blogspot.com በሚል ለአወናባጆቹ መልስ በመስጠት ላይ የተመሰረተ ብሎግ ብቅ ማለቱን ታስታውሳላች። ይህ ብሎግም እነዚህን ሰላም ሲፈጠር የሚያንቀጠቅጣቸውን እውነት የሚያስደንብራቸውን ግለሰቦች እጅጉን አሳሰባቸው። የስድብ ውርጅብኝ መሰነዛዛርም ተጀመረ ማለት ነው። መረዋምም እንዲሁ ለምእመናን መድረስ ያለበትን ለማዳረስ ይህንኑ የጀመሩትን የብሎግ መስመር በመጠቀም ስርጭቱን ጀመረ። በጥቂት ሳምንታት እስከ 10,000 ግለሰቦች የጎበኙት መረዋ የማይጋፉት ባላጋራ መሆኑ ታያቸው። ያነበቡት ሳይሆን ወደ ፊት ሊወጣ ይችል ይሆናል የሚሉት የማያውቁት አስፋራቸው። መቅበጥበጥ ጀመሩ። ለድሮው እምነት የሌለው ግለሰብ መሪው የወለቀ መኪና ማለት ነው ይባል ነበርና።
ውድ አንባብያን ሰሞኑን ደግሞ ትላንትና selame tewahedoን የሚመስል Bloge ፈጥረው ሊያወናብዱ የተነሱት እነዚህ ግለሰቦች ዛሬ Merewametta.blogspot.com የሚለውን ብሎግ በማስመሰል ከመሃከል ካለው ሁለት T አንዱን በማውጣት ሊያወንብዱ መነሳታቸውን በጅምላ E Mail እየላኩ ስናያቸው ገረመን። ለእውነት መቆም እንጂ ሃሰትን ከእውነት በማስጠጋት ሃሰት እውነት እንደማይሆን ግን የተረዱት አልመሰለንም። በበኩላችን መልካሙን እየተመኘንላቸው ልቦናቸውን ወደ እምነት እንዲመልስላቸው ከመጸለይ አናቌርጥም። እነዚህ ወንድሞች ደግሞ የሚታይ እውነትን እየካዱ ያላዩትን ማመን ቢከብዳቸው ምን ይገርመናል?
ወደ ሌላው እንመለስና በትላንትናው እለት ተጠርቶ በነበረው ስብሰባ የተገኘው ሕዝብ ያካሄደውን ስብሰባ ተከታትለን ነበር። ተሰብሳቢው ምእመን ቦርዱ የሚያደርገው ሁሉ ቤተክርስቲያንችንን ወደጥፋት እየመራው መሆኑን ሲያምን አሁንም እባካችሁ ብለን መነጋገር አለብንና ሄደን እናናገራቸው እነሱም እኮ ወንድሞቻችን ናቸው ብለው ሲወያዩ ለማድመጥ እድል አግኝተናል። የገረመን ስብሰባው ከቤተክርስቲያኑ ውጭ መደረጉ እንጂ ፈሪሃ እግዚአብሄር ያደረባቸው ግለሰቦች ለመሆናቸው አነጋገራቸውና ስነስርአት መጠበቃቸውን አይተን ተደስተናል። የተናገረ ይውጣ የሚል አልነበረም ፖሊስ አልተቀጠረም ስድብና ውርጅብኝ አልነበረም። ቤቱ የተስማማበትን ስራ ላይ ለማዋል የተመረጡት ወንድሞችና እህቶች ጉዞአቸው እንዲሳካላቸው ከመመኘት በስተቀር። ውሳኔውን ማቅረቡ የተመራጮቹን ሥራ መቅደም እንዳይሆን በመስጋት መረዋ እነሱ እስኪናገሩ ድረስ ከማተም ይቆጠባል። ተመራጮቹ ይፋ በሚያደርጉበት ሰዓት የበኩላችንን እንደምናበስራችሁ ቃል እንገባለን።
ለሽምግልና ሄደው ቦርዱን ያነጋገሩት ግለሰቦች ምን እንደተባሉ ለሕዝቡ ግልጽ እንደሚያደርጉም እምነታችን ነው።
እኛ ምኞታችን ቤተክርስቲያናችን ወደነበረበት እንዲመለስ ብቻ ነው። ምእመናን እንደጥንቱ የተነጠቁትን ቤተክርስቲያን ወደነበረበት የመመለስ ሃላፊነት አለባቸው ብለን እናምናለን። የሰባራ ህልሙ ምርኩ ማግኘት ነው ይላሉና?
ልትገናኙን ለምትፈልጉ ሁሉ ብሎጉ ውስት በመግባት መጻፍ እንደምትችሉ እየጋበዝን ከብሎግ ውጭ ለምትፈልጉን የ e-mail አድራሻችን በፊት እንደገለጽነው Yetayalewnetu@gmail.com መሆኑን በድጋሜ መግለጽ እንወዳለን።

  • የከርሞ ሰው ይበለን