Monday, February 1, 2010

ዝምታ በራሱ ተቃውሞ ነው። ቁጥር ፲

በትናንትናው ሰንበት ከቅዳሴ በኋላ ለአምልኮ ለመጣው ሕዝብ እንዲተዋወቁ የተደረገው አዲስ የቦርድ አባላት ለአምልኮ ለመጣው ሕዝብ እንዲተዋወቁ መደረጉን ከማስተዋላችንም በላይ፧ ሥራቸው የተቃና እንዲሆን በካህኑ መመረቃቸውን ለመታዘብ በቅተናል። ያልገረመን ነገር ቢኖር ግን ስማቸው ሲጠራም ሆነ ካህኑ በድጋሜ ተነስተው አጨብጭቡ ሲሉ እንኴን ያጨበጨበ አንድም ግለሰብ አለመኖሩ ነው። በቦርድ አባባል ቤተክርስቲያኑን መስርቶ እዚህ ያደረሰው የዳላስ አማኝ እኛ ያወጣንልህን "ሕገ መንግስት" ካልተቀበልክ ተብሎ ከአባልነት ተባሮ እያለ አሁንም በስሙ ጥቂቶች ሊቀልዱበት እንደ ደርግ ሆነው ሊያላግጡበት መነሳታቸውን ያየ ምን ዘመን ላይ ደረስን ቢል አንገረምም። መረዋም ሆነ ባካባቢ የተሰባሰቡ ግለሰቦች ይህንን እውነታ ከመድረሱ በፊት መዘገባቸው ይታወሳል እስካሁን ደግሞ ይሆናል ያልነው ሆነ እንጂ ምንም አዲስ ክስተት ተፈጥሮ አላየንም። ስማቸው ሲጠራ ለምን ምእመን አላጨበጨበም ሲባል እንደተለመደው ከመሃከላችን ያለው ቀላጅ " የሚዘረፈው ገንዘብ ብዛት ካሁኑ አስፈርቶት ነው" ማለቱን ሰምተን ዛሬም ስቀናል። አባባሉ ቅዳሜ ተደረጎ በነበረው አጠቃላይ "የቤተክርስቲያን አመታዊ ስብሰባ" ላይ የቀድሞው ሊቀ መንበር የቤተክርስቲያኑ ገንዘብ በቦርድ ተመራጮች እየተዘረፈ መሆኑን በዘገባቸው ላይ ጠቅሰውት የነበረውን ለማንሳት እንደሆነም ገብቶናል።

የተራበን ከብት ቡቃያ ውስጥ አስገብቶ አትጋጥ ማለት እንደማይቻል እየታወቀ ወይንም የወተት ማሰሮ መግላሊት ከፍቶ ድመትን ወተት አትቅመሺ ማለት የዋህነት መሆኑን እንዴት ሁሉም እንዳልገባቸው እያስገረመ በነበሩበት ይቆዩ ማለት ግን ስርቆትን ማጽደቅ ነው ብለን እናምናለን። በስብሰባ ላይ ተገኝተው የነበሩ አንድ አዛውንት የተናገሩትን በዚህ አጋጣሚ ልናካፍላችሁ እንወዳለን። እኚህ አባት ገንዘብ ተሰረቀ አልተሰረቀም የተባለውን ክርክር አዳምጠው አንዴ ልናገር በማለት ተነሱና የሚከተለውን ተረቱ። አንድ ግለሰብ ታመመና ወደ ዶክተር ዘንድ በመሄድ እራስምታት እያስቸገረው መሆኑንና መድሃኒት እንደሚፈልግ ዶክተሩን ቢጠይቀው ዶክተሩ በማዘን ወንደሜ አንተ እራስምታት ትላለህ ከዛ የባሰ ካንስር እየሰረሰረህ ነው አለው ብለው ዛሬ ተሰረቀ የተባለው $6000 ሳይሆን ከዛ የባሰ ችግር ቤተክርስቲያናችን ውስጥ እንዳለና የሚያሳስባቸው እሱ መሆኑን ተናገረዋል።

ወደ ትላንትናው ትርኢት እንመለስና አዲስ ተመራጭ ነን ባዬች የቦርድ አባላትን ያስተዋወቁት "የአስመራጭ ኮሚቴ" ተወካይ የተመራጮቹን ስም ጠርተው ካስተዋወቁ በኋላ የቤተክርስቲያናችን ችግር በዚህ እንደማይፈታ መናገራቸው ባይገርመንም ከዋለ ካደረ ሰው መማር እንደሚችል ግን እሳቸውን በማየት ለመታዘብ እድል ሰጥቶናል።

በትናንትናው እለት በተደረገው የቦርድ የውስጥ "ምርጫ" የስልጣን አሰላለፍ እንደሚከተለው ሆኖአል።

ሊቀ መንበር አቶ ዬሴፍ
ም/ሊቀምንበር አቶ ሙሉአለም
ጸሃፊ አቶ አበበ ጤፉ ሆነው ስልጣነ መንበር ሲረከቡ የቀድሞው ሊቀመንበር ከቦርድ እለቃለሁ ቢሉም በአስመራጭ ኮሚቴው አባላት ልመና ሃሳባቸውን እንደቀየሩ የውስጥ ምንጮቻችን ገልጸውልናል። ሂሳብ አጎደሉ የተባሉት የሂሳብ ዶክተርም ሆኑ የሳቸው ተባባሪ ነርስ መረጃዎችንና ዶሴዎችን ለማጥፋት እንዲችሉ በነበሩበት እንዲቆዩ መደረጉን ልናወሳችሁ እንወዳለን።

ባለቤታቸው ከስልጣን የተባረሩባቸው ግለስብም በቦርድ መካከል የተነሳው መበጣበጥ እንዲቆም መማጸናቸውን ስናዳምጥ ከልብ ማዘናችንን መግለጹ ተገቢ ይመስለናል። ምን አልባት የቀድሞው ሊቀመንበር ከስልጣን ከለቀቁ እንደሚወራው አቶ ብዙአየሁም እንዲሁ በቃኝ ካሉ ባለቤታቸው እንደገና ወደ ቦርድ የመግባት እድል ይኖራታል ብለው አስበው ሊሆን እንደሚችል ግን ለመተንበይ አልተቸገርንም።

መረዋ ዛሬ ለሁላችንም አንድ መልእክት ማስተላለፍ ይወዳል።

ቤተክርስቲያናችን ወደ መፍረሱ እየተቃረበ ለመሆኑ ሁሉም የተስማማበት ጉዳይ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት። ይህንን መጥፎ ሂደት ለመግታተ የሚቻለው የሚከተሉት ማረሚያውች ባፋጣኝ ሲደረጉ ብቻ ነው ብሎ ያምናል።

1 ቦርዱ በጊዚያዊ ኮሚቴ ሲተካ
2 የቀድሞ አባላት ወደ አባልነታቸው እንዲመለሱ ሲፈቀድ
3 ተቀየረ የተባለው የአንባገነን ሕግ ተሽሮ ወደ ድሮው ሕግ ስንመለስ
4 ቤተክርስቲያኑ የአምልኮ እንጂ የፖለቲካ ስፍራ መሆኑ ሲቆም
5 የእምነትን ጉዳይ ካህናቱ ብቻ መምራት ሲችሉ
5 የቤተክርስቲያን ገንዘብ የሰረቁ ምህረት ሲደረግላቸው ብቻ ነው ብለን እናምናለን። ይህ ካልሆነ ቀጣዩ ትግል በዝምታ መሆን አይችልምና ዝምታ በራሱ ተቃውሞ መሆኑ ቢገባንም ተሰብስበን በመነጋገር መፍትሄ መፍጠር አለብን በማለት ጥሪ ማድረግ እንወዳለን።

አላዛርን ከመቃብር ያስነሳ አምላክ የመቃብር ድንጋይ መፈንቀል አላቃተውም የሕዝብን ተሳትፎ በመፈለግ ግን"የመቃብሩን ድንጋይ ፈንቅሉ" አለ እንጂ። ስለሆነም ክርስቲያናዊ ግዳጅ አለብንና አሁንስ በዛ መበያው ወቅት ዛሬ ነው እንላለን።