Monday, December 13, 2010

የተደናቀፈ ሰው አጠገቡ ያለውን ይዞ ይወድቃል ቁጥር ፶፪

ቴክሳሶች አንድ መኪና ላይ የሚለጠፍ መፈክር አላቸው። IF YOU GO TO HELL DON'T BLAME IT ON JESUS  "ሲኦል ብትገባ በክርስቶስ አታመካኝ" የሚል ነው። ወደ ገሃነም እንዳትገባ ክርስቶስ ላንተና ለኔ ሐጥያት ደሙን እስከማፍሰስ ደርሷልና  ማለታቸውም ነው። ታዲያ

ለሠራንው ምስጋና እንደምንቀበል ሁሉ  ለጥፋታችንም ሃላፊነት መውሰድ ካልቻልን ደካሞች ነን።
ስለሌላ ሰው ድክመት ማውራት ቀላል ነው ስለራስ ድክመት መናገር ግን ቆራጥነትን ይጠይቃል።
ሰው ያልዘራውን አያጭድም።
አለማወቅን መቀበል አዋቂነት ነው።
በንስሐ የማያምንን ሰው ቅስፈት አለ  ብሎ  ለማስተማር መሞከር የዋህነት ነው።

ውድ የመረዋ አንባብያን። የቤተክርስቲያናችን ችግር እየባሰ እንጂ እየተሻለው እንዳልመጣ ምስክሮቹ እናንተው ናችሁና መናገር አስፈላጊ አይመስለንም። ፍቅራችን የትሄደ? ብሎ ለጠየቀ አንድ ወንድም "አሁንስ ድሮም እንደነበር እየተጠራጠርኩ ነው።" ያሉት እናት ተስፋ ቆርጠው ለመናገራቸው ጠቋሚ አላስፈለገንም። እኚህ በየሳምንቱ በማዶው ጦማር ስማቸው እየተጠቀሰ የሚሰደቡትን አዛውንት ለመሆኑ ጥንካሬና ትእግስት ከየት አመጡ? ተብለው ሲጠየቁ ጠዋት ከምደግማት ውዳሴ  ማርያም  ማታ ከማነበው መጽሐፍ ቅዱስ ነዋ ልጄ ማለታቸውን የነገረን በቅርብ የሚያውቃቸው ጓደኛቸው ነው። ገንዘባቸውን ባፈሰሱ፤ ቀሳውስቶችን በረዱ፤ አበስ ገበርኩ ብለው ሥጋወደሙ በተቀበሉ የዚህ ቤተክርስቲያን አመራር ደጋፊዎች ነን ባዬች በየጦማሩ ሲያብጠለጥሏቸው፤ ከትዳራቸው ሊያፋቱ፡ ቤተሰባቸውን ሊበትኑ ሲዘምቱ "ፍቅር ብናሳያቸው እናሸንፋቸዋለን" ብለው ተሰዳቢው መልስ ሲሰጡ መስማት ላዳማጭ ውሸት ቢመስል ምን ይገርማል። ነገሩ ግን ባይገርማችሁ እውነት ነው።

የሰደቧቸው ሰዎች የሰደቡት ሁላችንንም ነው። የተሳደቡት የከተማውን አንጋፋዎች ነው። የተሳደቡት እራሳቸውን ነው። "ጎጃሜ ነኝ የሚለው ዘሩ ትግሬ የሆነ" ሲሉ የተባለው ግለሰብ የትግራይ ተወላጅ አለመሆኑን ስላወቅን ብቻ  ሳይሆን ቢሆንስ ከትግራይ መወለድ ሃጥያት ነውን? ብሎ  የሚጠይቃቸው ሰው የጠፋው ነገ  እኔን ደግሞ  ብናገር ያልተወልድኩበትን ሰፈር ይለጥፉብኛል ብሎ  በመስጋት ይመስለናል። ከተወሰነ ብሔር መወለድ ክብር የሚመስላቸው አሁንም ከዘር አረንቋ ውስጥ የተዋጡ ጊዜአቸው ያለፈባቸው ትምክህተኞች ብቻ  ናቸው።

ፖለቲከኛ ለመሆን እኮ እውቀትን ይጠይቃል።
ለዘረኝነት ግን መሃይምነት መፈልፈያ ቅርጫቱ ነው።

በዛሬው ምሽት የምስራች ይዘንላችሁ አልቀረብንም። የደሰታ መረዋ ልንመታ አልተነሳንም። የሃዘን ማቅም አላጠለቅንም። እንዳንናገረው እየፈራን እንዳንተወው እያናደደን ይዘንው ቀረብን እንጂ። ነገሩ እንዲህ ነው።

የሚካኤል ደብር አስተዳዳሪ ቦርድ ጸሐፊ የሆኑት አቶ  አበበ (ጤፉ) ባለፈው ዓርብ እለት ከፍርድ ቤት ውሎ ምሽት መሆኑ ነው: የመንገድ ሴትኛ አዳሪ ሲያነሱ ተገኝተው ታስረው እንደነበር የዳላስ ፖሊስ በድህረ ገጹ ላይ ከነፎቶግራፋቸው እንዳወጣ ተደውሎ  ሲነገረን ያልነው ነገር ቢኖር "ሚካኤል እውነትም ተቆጥቷል" የሚል ነበር። በተለይም ድርጊቱ ተፈጸመ  የተባለው በቀጠሮው ቀን መሆኑ ሁላችንንም ሳያስገርም አልቀረም። አቶ አበበ ዓርብ ታስረው እሑድ ከቤተክርስቲያን መጥተው የምእመናንን  ዓይን እያዩ  ማስታወቂያ መናገራቸው ቢገርመንም የሳምንቱ እሑድ ሳይደርስ የተከበረ  ቤተክርስቲያናችንን እንደተከበረ  እንዲኖር ባስቸኳይ ከሃላፊነታቸው እንዲለቁ መረዋ  ምክሩን ይለግሳል። የተደናቀፈ ሰው አጠገቡ ያለውን ይዞ ይወድቃልና፡ አብረው ያሉትም የቦርድ አባላት ሰላሙን ለመፍጠር በፈቃዳቸው ቢሰናበቱ ለሚመጣው ችግር መፍትሄ ይሆናል ብለን እናምናለን።

መረዋ ለአቶ  አበበ ጽናቱን እንዲሰጣቸው ይጸልያል።

ከፈተና ያድናችሁ።