Wednesday, December 29, 2010

በሐዘን የሚቀልድ ደካማ ሰው ብቻ ነው። ቁጥር ፶፬

ውድ የመረዋ አንባብያን ሰሞኑን የደረሰብን ሐዘን መሪር ነበር።  ሁሉም በወጣቱ ልጃችን በማትያስ ከበደ ብርሃኑ ሞት እጅጉን ለማዘኑ በወቅቱ ተሰብስቦ የነበረውን ምእመን ለቅሶ በማየት መገመት ይቻል ነበር። ወጣቶችና ሕጻናት ከመካከላቸው የተለየውን ጨቅላ ለመሰናበት ተሰብስበው የተናገሩትን ሁሉ ስናስታውስ ልጆቻችን ከኛ የተለየ አመለካከት፤ ከእኛ ዘንድ የራቀ ፍቅር እንዳላቸው አየንና በነሱ ተስፋ ተጽናናን። የቤተክርስቲያኑ መሪዎችም ልባቸው በሐዘኑ ተነክቶ የቤተክርስቲያኑን  አዳራሽ መፍቀዳቸውን ስናይ ደግሞ ሚካኤል ዋጋቸውን ይክፈላቸው እንዳልን ሁሉ በሐዘንም ፖለቲካ ሲጠቀሙ ማየታችን ግን አሳዝኖናል። ሊነበቡ የተዘጋጁትን ጽሑፎች እንዳይነበቡ  መከልከል አግባብ አልነበረም። ጽሑፉን ያዘጋጁትን ግለሰቦች ለመቅጣት በማሰብ ሃዘንተኛውን አብሮ መቅጣት በኛ አመለካከት ትክክል አልነበረም። አቶ አበበ ጤፉና አቶ ሙሉአለም ስለ ግለሰቦች ከመፍረዳቸው በፊት እራሳቸውን ቢያስተውሉ ኖሮ   እንደዚያ አይነት ውሳኔ ላይ ባልደረሱም ነበር።  ሰውን በፍቅር እንጂ በጥላቻ ማሸነፍ አይቻልም። ያም ሆነ ይህ ሐዘኑን ተወጣነው። በድጋሜ ዛሬም ለልጃችን ዘለዓለማያዊ እረፍትን ለወላጆቹ ጽናትን ለቤተሰብና ጓደኛ ብርታትን እንለምናለን።

በዚሁ ባለፈው ሳምንት ለብዙ ጊዜ አብረውን የነበሩ እናታችን ወይዘሮ ሰናይት ኃይሌም ከመካከላችን ተለይተውናል። ከጅምሩ የዚህ ቤተክርስቲያን መስራች የነበሩት ወይዘሮ ሰናይት ኃይሌ ለዳላስ ሚካኤል ያበረከቱት አስተዋጽኦ ቀላል አልነበረም። ልጆቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ጭምር ለሚካኤል እድገት አስተዋጽኦ ያደረጉ ግለሰቦች ሥም ሲጠራ የመጀመሪያውን ስፍራ እንደሚይዙ የማይስማማ  ግለሰብ ቢኖር የቤተክርስቲያናችንን ታሪክ የማያውቅ ወደ ከተማችን በቅርቡ ጎራ ያለ ብቻ ይሆናል።  ለወይዘሮ ሰናይት መንግስተ ሰማያትን ለልጆቻቸውና ቤተሰባቸው  መጽናናትን መረዋ  እየተመኘ፡ የሐዘናቸው ተካፋይ እንደሆነም  ይገልጻል።

ይህንን ካልን ዘንዳ፡

በዛሬው እለት የምናስነብባችሁ የዳላስ ምእመን በመላ በሐዘን ላይ እያለን የቦርድ ደጋፊዎች ነን የሚለው ጦማር (BLOGS)በገጹ ላይ የለጠፈውን ጽሑፍ ነው። ጽሑፉን እንዳለ ገልብጠን ለአንባብያን አቅርበነዋል። ከዚህ በታች ያለውን አንብቡና ፍቀር እምነት እያሉ የሚሰብኩን አስመሳዮች ለሐዘን ደንታ የሌላቸው ፈሪሃ እግዚአብሔር የራቃቸው ለመሆናቸው ምስክር የሆነውን ብእራቸውን እዩላቸው።እኛ ባባላቸው ካዘንን በ ድርጊታቸው ከተጸጸትንላቸው ቆየን። የጻፉት ጽሑፍ ከዚህ በታች አቅርበንላችኋል መልካም ንባብ። 
[Post a Comment On: Dallaseotc"የተጀመረው መሻሻል ከግቡ እንዲደርስ"




2 Comments - Show Original Post

በጎረቤታችን ላይ የተንኮል ተግባር ከመፈጸማችን በፊት በአምላክ ፊት ምን እንደሚጠብቀን አስቀድመን ብናውቅ ሁላችንም የመጀመሪያውን ድንጋይ ለመወርወር ባልቃጣን ነበር። በዚህ በያዝነው ሳምንት ውስጥ ፈጣሪያችን አምላካችን ለ ዳላስ አካባቢ የክርስቶስ አማኞችና የቅዱስ ሚካኤል ምእመን ብዙ ተአምር አሳይቶናል። እንድንጠነቀቅም ፊታችንንም ወደ ፈጣሪያችን እንድንመልስ ሊያደርገን ሁለት ተአምር አሳይቶናል። አንደኛው የቤተክርስቲያናችን አባል የሆነው ጸሃፊያችን የልቡን አይቶ ሃጢአት ውስጥ እንዳይገባና እንዳይረክስ መልአኩን በ ፖሊስ መልክ ልኮ ከ መጥፎ ተግባር እንዲድን አድርጎታል።




ባኳያውም የዚህን ግለሰብ ኅጢአት ከፖሊስ ሰነድ ውስጥ አውጥቶ በየታክሲያችን ላይ ሲበትንና ያገሩን ልጅ ስም ሲያጠፋ የነበረው ( ስሙን በደረሰበት አደጋ ምክንያት ለመጥቀስ በማንፈልገው ግለሰብ ) ላይ በደረሰው የአባት ሃጢአት ለልጅ በተላለፈ አደጋ ልጁን ያጣው ሰው የቅዱስ ሚካኤልን ደጀ ሰላም መጥናኛ እንዲሆን ያውም በትምህርት ቀን ያስፈቀደለት ማን ይመስላችኋል!


መድረኩን ማስፈቀድ ብቻ ሳይሆን ቀሳውስቱና ዲያቆናት እንዲተባበሩ ለማድረግ ብዙ ጥረት ያደረገው ሰው ነው። አሱም ፤በ እኔ ላይ የራሱን ጉድ ደብቆ ልጆቹን በትኖ ብህግ ያገባት ሚስቱን የልጆቹን እናት


ጥሎ ወደ ሴተኛ አዳሪ ቤት የገባ ሰው የኔን ሃጢአት እያጋነነ ለጠላት ስለሰጠብኝ ብሎ አልተቀየመውም። ይሄን ያልነው እኛ ጉዱን የምናውቅ ነን። ይልቅስ በማያውቀው ሓጢአት ዉስጥ ገብቶ ልጁን ማጣቱ አሳዝኖት እንደማንኛችንም ሲያለቅስ አምሽቷል። ታዲያ እኛ እን ማን ሆነን ነው የቅዱስ ሚካኤልን ሥራ ነገ በኛ ላይ የሚደርሰውን አዉቀን የሰው ስም ለማጥፋትና በሃሰት ሰው ለመክሰስ እምንመኘው።


ለዚህ ነው ነገ የሚደርስብንን ብናውቅ ዛሬ እማጥ ውስጥ አንገባም ነበር ያልኩት። በሰው ላይ ተንኮል ለመስራት አንሯሯጥ ሰው ባያውቅብን እግዚአቤሔር ያውቀዋልና፤ ከሱ የሚሸሸግ ነገር እንደሌለ እንወቅ።


አሜን;






December 18, 2010 1:52 PM]

ይህ የኛ ሳይሆን የአስተያየት ሰጭዎች ነው ሊሏችሁ ይነሱ ይሆናል። እውነቱ ግን እነሱ አንብበው ያጸደቁት ብቻ እንደሚወጣ እራሳቸው የሚክዱ ካለመሆኑም በላይ በጦማራቸው BLOGS በአስተያየት መስጫ አምዳቸው በግልጽ ሃላፊነት እንደሚወስዱበት አንብበው እንደሚለጥፉት የተጻፈ ነው። 
እነዚህ ከሆኑ የእምነት ሰዎች በእውነት ብዙ የሚያነጋግረን ጉዳይ አለን። እነዚህ ከሆኑ የመሪዎቻችን ደጋፊዎች ወንድሞቼ ቤታችንን ለማፍረስ ትልቅ ትግል እየተካሄደ ነው። እነዚህ ከሆኑ የቤተክርስቲያናችን አንጋፋዎች ቤተክርስቲያናችን ሽማግሌ የለበትም የሚያሰኝ ነው። ይህ ከሆነ ሐዘንተኛን ማጽናናት ወንድሞቼ ለእናንተው ፍርዱን እንተዋለን። በባህላችን ከምንም በላይ ሃዘንን እናከብራለን። ያንን የማይቀበል ስለሐዘን ደንታ  የሌለው ብቻ  ነው። በመሳደብ ለወጥ ሲመጣ አላየንም። በማስፈራራት ደግሞ ፍቅር አይገነባም።   

የሳምንት ሰው ይበለን።